Friday, May 15, 2015

አንገት ቆራጮቹ አይ ኤስ አይ ኤስ  የሚለብሱት “ጥቁር” ልብስ እና እንዲሁም “ብርቱካናማ” ልብስ አልብሶ የሚያርዳቸው ሰዎች የልብሶቹ ከለሮች ሚስጥር ምን እንደሆነ ያውቃሉን?

isis

በቅርቡ የአክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) አንገት ቆራጮች ብዙ ሰዎች የማይጠይቁት አንድ ጥያቄ አለ እርሱም ምንድ ነው? ለምንድ ነው የኢስላም ጂሀዲስት የሆነው አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) አንገታቸውን የሚቆርጣቸውን ሰዎች ብርቱካናማ ልብስ የሚያለብሳቸው? እንዲሁም አክራሪዎቹ የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) አንገት ቆራጮች ጥቁር ልብስ የሚለብሱት? የሚለውን ጥያቄ መጠየቅ ያስፈልጋል:: በአብዛኛው በአለም ላይ ኦሬንጅ ከለር ያለው ልብስ በብዙ ሰዎች መካከል ይመረጣል:: በተጨማሪም ከሌሎች ከለሮችም ደምቆም ይታያል:: ስለሆነም በሁለቱ ከለሮች ማለትም በኦሬንጅ እና በጥቁር ቀለም ውስጥ የተደበቀ የሚስጥር ፍቺ አለ:: በመጀመሪያ የሚቀድመው ብርቱካናማው ቀለም ሲሆን የሚቀጥለው ደግሞ ጥቁር ቀለም ነው:: ይህ ቀለም እየኖርን ያለንበትን አለም ያመለክታል:: ይህ ማለት ምንድ ነው አለማችን በመጀመሪያ ለመብላት እንደ ሚያስጎመዥ እንደ በሰለ ብርቱካን ስትመስል ፍጻሜዋ ግን ጥቁር ድቅድቅ ጨለማ ነው:: ለዚህ ነው አንገት ቆራጮቹ አክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) ሚኒሻዎች የሚለብሱት ጥቁር ልብስ የሚወክለው የመጨረሻውን የዚህን አለም የሰይጣን መንግስትን ሲሆን ብርቱካናማ ልብስ አልብሰው የሚያርዷቸው ሰዎች ደግሞ የሚወክሉት ደግሞ ለሰይጣን የሚቀርብ የደም መስዋእት ግብር ነው::
“ታላቁ የእግዚአብሔር ቀን ቀርቦአል፤ የእግዚአብሔር ቀን ድምፅ ቀርቦአል እጅግም ፈጥኖአል፤ ኃያሉም በዚያ በመራራ ልቅሶ ይጮኻል። ያ ቀን የመዓት ቀን የመከራና የጭንቀት ቀን፥ የመፍረስና የመጥፋት ቀን፥ የጨለማና የጭጋግ ቀን፥ የደመናና የድቅድቅ ጨለማ ቀን፥ በተመሸጉ ከተሞችና በረዘሙ ግንቦች ላይ የመለከትና የሰልፍ ጩኸት ቀን ነው። በእግዚአብሔርም ላይ ኃጢአት ሠርተዋልና እንደ ዕውር እስኪሄዱ ድረስ ሰዎችን አስጨንቃለሁ፤ ደማቸውም እንደ ትቢያ፥ ሥጋቸውም እንደ ጕድፍ ይፈስሳል። በእግዚአብሔርም ቍጣ ቀን ብራቸውና ወርቃቸው ሊያድናቸው አይችልም፤ እርሱም በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ፈጥኖ ይጨርሳቸዋልና ምድር ሁሉ በቅንዓቱ እሳት ትበላለች።” ሰፎ 1 : 14-18
1
ብርቱካናማውን ቀለም ያለበትን ልብስ የሚያዘወትሩ የአለማችን አያሌ ታዋቂ የቲቪ እና የሚዲያ አክተሮችን ብንጠቅስ ኦፕራ ዊንፍሬይ፣ ኬቲ ፔሪ ፣ ሪሃና እና ቢዮንሴ ላውረንስ እንዲሁም አለም አቀፍ ፓለቲከኞች መካከል ሂላሪ ክሊንተን እና ሚችል ኦባማ በተጨማሪም ከታዋቂ ቴሌቨዥን ፕሮግራም Orenge Black በተጨማሪም የተራውና የብሄራዊው የፓለቲካ እስር ቤት የታራሚዎች እና የወንጀለኞች ደንብ ልብስ እንዲሁም አለም አቀፉ እስር ቤት “ጓንታናማው” የታራሚዎች የደንብ ልብስ በመጨረሻውም የታሪከኛው አንገት ቆራጩ የአክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) የታራጆቹ ልብሶች የብርቱካናማው ቀለም ሚስጥራዊ ልብሶች ናቸው::
በኦሬንጅ እና በጥቁር ቀለም ውስጥ በሰይጣን የተገለጡት ሚስጥሮች በማቀናጀት የሰዎችን አይምሮ ማግዛት እና ማስጨነቅ ዋናው አላማ ነው::
የብርቱካናማው ቀለም የሚስጥር ቁልፍ ሲገለጥ
ORANGE የሚለው ቃል ፊደሎች በቁጥር ሲለወጡ የሚሰጡት የቁጥር ድምር ውጤት
2
የጥቁር ቀለም የሚስጥር ቁልፍ ሲገለጥ
Black የሚለው ቃል ፊደሎች በቁጥር ሲለወጡ የሚሰጡት የቁጥር ድምር ውጤት
3
የብሩትካናማው ቀለም ያለበትን ልብስ የሚለብሱ ታዋቂ ያለማችን ሰዎች የመንግስት ተቋማቶች እንዲሁም ለተለያዩ ክብረ በአል ላይ የሚለበሱ እና ለክብረ በአሉ ስነስርአት የሚውሉ ብርቱካናማውን ቀለም የያዙ ማናቸውም ቁሳቁሶች የልጆች መጫወቻዎችን ጨምሮ በተጨማሪም የአክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) ጨምሮ ብርቱካናማውን ቀለም ለብሰውና አስለብሰው ሲታዩ እና ሲያሳዩ ከክፋት አምላክ እና አባት ከሆነው ከዲያብሎስ መንግስት ጋር ህብረት ማድረጋቸውን ያመለክታሉ::
36096_halloween
ብርቱካናማውን ቀለም በአሁን ግዜ በመጨረሻው ዘመን በይፋ የተፈጠረውን አዲሱ የአለም መንግስት ስርአትን ( NEW WORLD ORDER ) ወይንም የኢልሚናቲ 666 መንግስት የሚስጥር ቀለም ነው:: አንድ ብርቱካናማውን ቀለም ያለበት ልብስ ላይ የሰው ደም ከነካው ለሰይጣን መስዋእት ተደርጎ በትክክል ተፈጽሞዋል ተብሎ ይታመናል:: እንዲሁም ጓንታናማው አሰቃቂ እስር ቤትን ጨምሮ አብዛኛው በአለም ላይ ያሉ እስር ቤቶች ብርቱካናማውን ቀለም ልብስ ታሳሪዎቹ ካስለበሱዋቸው ቡኋላ አሰቃቂ ቅጣት በሁሉም ላይ ያደርሱባቸዋል በተጨማሪም ብዙዎቹ እስር ቤት ወስጥ Guillotine በተባለ መሳሪያ አንገታቸው እዛው እስር ቤት ውስጥ ተቀልቶዋል:: ወደ ፊትም ይቀላል::
USA_DetaineesWEB
ዛሬ በአለማችን ላይ የብሩትካናማው ቀለም አብዮት ያስጀመሩት ምእራባውያን በዬክሬን ውስጥ እንደ ፈረንጆች አቆጣጠር 2004 ላይ “ብርቱካናማው አብዮት” በሚል መጠሪያ የመጀመሪያው ህዝባዊ አመጽ በዩክሬን አስጀመሩት ከዛ ቀን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ ዩክሬን በብሩትካናማው እሳት እየነደደች ትገኛለች:: የአክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) ከጊዜ ወደ ግዜ የሚያርዳቸውን ሰዎች በብሩትካናማው ልብስ አስለብሶ አንገታቸውን በካራ ይበጥሳቸዋል:: ስለዚህ ብሩትካናማው ቀለም የሚወክለው ሰይጣንን 666 ሲሆን ጥቁሩ ቀለም ያለው ልብስ የሚወክለው የዚህ አለም ገዥዎች የሚጠቀሙበት ድንገተኛ የስልክ አደጋ ጥሪ ቁጥር የሆነውን 119/911 ያመለክታል:: በተጨማሪም የአክራሪው የኢስላም ጂሀዲስት አይ ኤስ አይ ኤስ (ISIS) የፈጠሩት እና በተለያዩ ቁሳቁስ የሚረዱት ታላላቆች የምእራባውያኖቹ መንግስታት ለሁሉም ነገር መፈጠር ዋናዎቹ ባለድርሻ አካላት ናቸው:: ለዚህም ነው በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ስለመጨረሻው ዘመን ስለምትገለጠው እና በሰዎች ደም ሰክራ የምትታየው “ታላቂቱ ጋለሞታ” የምድር እርኩሰት ይህ የመጨረሻው ዘመን ታላላቆቹን የምድር ነገስታትና እና መንግስትን የብሩትካናማው ቀለም ድብቅ ሰይጣናዊ ሴራቸውን ያመለክታል::
25B628A500000578-2955345-image-m-4_1424077667026
“ሰባቱንም ጽዋዎች ከያዙ ከሰባቱ መላእክት አንዱ መጥቶ። ና በብዙም ውኃዎች ላይ የተቀመጠችውን የታላቂቱን ጋለሞታ ፍርድ አሳይሃለሁ፤ የምድርም ነገሥታት ከእርስዋ ጋር ሴሰኑ በምድርም የሚኖሩ ከዝሙትዋ ወይን ጠጅ ሰከሩ ብሎ ተናገረኝ። በመንፈስም ወደ በረሀ ወሰደኝ፤ የስድብም ስሞች በሞሉበት፥ ሰባት ራሶችና አሥር ቀንዶችም ባሉበት በቀይ አውሬ ላይ አንዲት ሴት ተቀምጣ አየሁ። ሴቲቱም በቀይና በሐምራዊ ልብስ ተጐናጽፋ በወርቅና በከበሩ ድንጋዮች በዕንቈችም ተሸልማ ነበር፥ በእጅዋም የሚያስጸይፍ ነገር የዝሙትዋም ርኵሰት የሞላባትን የወርቅ ጽዋ ያዘች፤ በግምባርዋም ምስጢር የሆነ ስም። ታላቂቱ ባቢሎን፥ የጋለሞታዎችና የምድር ርኵሰት እናት ተብሎ ተጻፈ። ሴቲቱም በቅዱሳን ደምና በኢየሱስ ምስክሮች ደም ሰክራ አየኋት። ባየኋትም ጊዜ እጅግ ታላቅ ድንቅ አደነቅሁ። መልአኩም አለኝ። የምትደነቅ ስለ ምንድር ነው? የሴቲቱን ምስጢርና የሚሸከማትን፥ ሰባት ራሶችና አስር ቀንዶች ያሉትን የአውሬውን ምስጢር እኔ እነግርሃለሁ። ያየኸው አውሬ አስቀድሞ ነበረ፥ አሁንም የለም፥ ከጥልቁም ይወጣ ዘንድ አለው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል፤ ስሞቻቸውም ከዓለም ፍጥረት ጀምሮ በሕይወት መጽሐፍ ያልተጻፉ በምድር የሚኖሩ አውሬው አስቀድሞ እንደነበረ አሁንም እንደሌለ፥ ነገር ግን እንዳለ ሲያዩ ያደንቃሉ። ጥበብ ያለው አእምሮ በዚህ ነው። ሰባቱ ራሶች ሴቲቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራራዎች ናቸው፥ ሰባት ነገሥታት ደግሞ ናቸው፤ አምስቱ ወድቀዋል አንዱም አለ፥ የቀረውም ገና አልመጣም፤ ሲመጣም፥ ጥቂት ጊዜ ሊቆይ ይገባዋል። የነበረውና የሌለውም አውሬ ራሱ ደግሞ ስምንተኛው ነው ከሰባቱም አንዱ ነው፥ ወደ ጥፋትም ይሄዳል። ያየሃቸውም አስሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አስር ነገሥታት ናቸው፥ ዳሩ ግን ከአውሬው ጋር ለአንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ። እነዚህ አንድ አሳብ አላቸው፥ ኃይላቸውንና ሥልጣናቸውንም ለአውሬው ይሰጣሉ።” ራዕ 17: 1:13

Sunday, May 10, 2015

ድር ድሮ የብልጽግና ወንጌል ሰባኪዎች ከአሜሪካን ነበር ወደ ኢትዮጵያ የሚጎርፉት። አሁን አሁን ደግሞ የተቸገርነው እኛ የሰለቸንን የብልጽግና ወንጌል ከኢትዮጵያ ተጋብዘው የሚመጡት ሰባኪዎች አይናቸውን በጨው አጥበው ሊሰብኩን መዳፈራቸው ነው። የኢትዮጵያ አብያተ ክርስትያናት ህብረት ይህንን ትምህርት ካወገዘች እንኳን አመታት አልፈውል። እንዴት ነው ነገሩ። አሁንማ በመድረክ ላይ ቆመው የገንዘብ መላክያ ፖስታ እያውለበለቡ አትለፉኝ ማለት የቀራቸውንም ማየት ጀምረናል። አልፈው አይን ሲያወጡም የዲያስፖራ  ምእመን አይን አውጥተህ ካለመንክ አይሰጥም ብለው መናገርም  ጀምረዋል። ይመስለኛል የብልጽግና ተኮር ሰባኪዎችን የገንዘብ አሰባሰብ ዘዴ (ድሮ በአለም እያለን በአራዳ ቋንቋ ፈለጣ ነበር የሚባለው)  ለጥቂት ጥቅም መልካም ነው በማለት የዋሆቹ እያዳቀሉት ይመስለኛል። አዲስአበባዎች አደብ ግዙ እንጂ።  እረ ወንጌልንና መልካም አስተማሪዎቻችሁን  አታሰነቅፉ።  እስቲ  የአዲስ አመት ኮንፍረነስ ለመካፈል ቤተክርስቲያን ሄደው አንዳንዶች የታዘቡትን ከፌስቡክ ላይ በተስፋዬ ተሰማ የተጻፈውን እናስነብባችሁ።

ትላንት ማታ የአዲስ አመት ኮንፍረነስ ለመካፈል ቤተክርስቲያን ሄጀ ነበር። ከኢትዮጵያ የተጋበዘው ሰባኪ የሚያስተምረው ስለእምነት ነበር። በርግጥ ይሄ ትምህርት የሰባኪው የራሱ ትምህርት አይደለም። የዚህ አይነቱ የእምነት ትምህርት አዲስ የመጣ እና ብዙ መፅሀፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ነገሮች የታጨቁበት የዘመኑ ብልጣብልጥ ሰባኪያን በአለም ዙሪያ ገንዘብ ለመሰብሰብ የሚጠቀሙበት፤ የኛ ሀገር ሰባኪወች ደግሞ የዚህ ጥቅም ተጋሪ ለመሆን የሚያራግቡት ትምህርት ነው ተበሎ በብዙ የሰነ መለኮት ምሁራን እና ክርስቲያኖች ይታመናል።
ተጋባዡ ሰባኪ የሚሰብከውን የእምነት ትምህርት ያጠናክርልኛል ብሎ የተለያዩ የመፅሀፍ ቅዱስ እና የሳይንስ ምሳሌዎችን እንግሊዝኛ እየቀየጠ ቢያስተምርም በመንፈሳዊዉም ሆነ በሳይንስ ጉዳዮች ዙሪያ ያነሳቸው ነጥቦች ግራ የሚያጋቡና እርስ በርስ የሚጣረሱ ሆነውብኝ ከቤተክርስቲያን ወጣሁ።
በስብከቱ ላይ ብዙ አደናጋሪ መልእክቶች በመተላለፉቸው ሁሉንም አንስቼ ስለማልዘልቅ ከተናገራቸው አይነተ ብዙ ስህቶች አንድ ከመንፈሳዊ አንድ ከሳይንሳዊ ስህተቶች ቀንጭቤ ልናገር። ሰባኪው አሰተምርበታለሁ ያለው ርእስ የእምነት ህጎች የሚል ነው።እንደ ሰባኪው አባባል “እኛ የእግዚአብሄር ልጆች ነን፣ የምንኖረው በአዲስ ኪዳን ዘመን ነው፣ በጌታ ካመንን ስራ ሳንሰራ እንበለፅጋለን፤ ስራ መስራት እርግማን ነው ደግሞም የብሉይ ኪዳን ህግ ነው።”
ሰባኪው በተጨማሪም “እስካሁን ያልበለፀግነው ስለማናምን እና ያመነውን ነገር ስለማንናገር ነው። ገንዘብ ለፖስተሮች እና ለቤተክርስቲያን አለመስጠታችንም ሌላው በድህነት የመኖራችን ምክንያት ነው” ይለናል።፡መልእክቱ ባጠቃላይ ስራ አትስሩ ገንዘብ አምጡ ነው።
ስለ እግዚአብሄር በረከት፣ ተግቶ ስለመስራት እና ሰለመበልፀግ መፅሀፍ ቅዱስ በበርካታ ክፍሎች የሚናገረው እውነት ግን ሰባኪው ካለው ነገር ጋር ፍፁም ተቃራኒ ነው።፡በርግጥ እኛ የግዚአብሄር ልጆች ነን። እግዚአብሄር ሰውን ይባርካል። ነገር ግን ሰው የሚባረከው ቢሊየነር ነኝ ብሎ ሰለጮኸ እና ሰለ ፎከረ አይደለም።፡ይህን ትምህርት የሚያሰተምሩት ሰወች ለምን እናንተ ቢሊየነር አትሆኑም ተብለው ሲጠየቁ በእምነት አርግዘናል ይላሉ መቸ እንደሚወልዱትም አይታወቅም።
ሰው የሚባረከው ያለፅድቅ በሆነ ባዶ ፋከራ ሳይሆን የእግዚአብሄርን ፅድቅ በመፈለግ እና በስራ ነው። ሰባኪው እንደሚለው ሰራ መስራት እርግማንና የብሉይ ኪዳን ህግ ብቻም አይደለም።፡ከአዲስ ኪዳን 27 መፅሀፍት 13ቱን የፃፈው ሀዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በአዲስ ኪዳን የእግዚአብሄር ልጆች ለሆንን ክርስቲያኖች በ2ኛ ተሰሎንቄ ምእራፍ 3: ከቁጥር 8 እሰከ 13 ላይ ” ከናንተ ዘንድ በአንድስ እንኩዋን እንዳንከብድበት ሌሊት እና ቀን በድካም እና በጥረት አየሰራን እንኖር ነበር,…..ደግሞም ከናንተ ጋር ሳለን ሊሰራ የማይወድ አይብላ ብለን አዘናችሁ ነበር” በማለት ክርስቲያኖች ሰራ እንዲሰሩ ግድ ብሎአል።
ቅዱስ ጳውሎስ የሰራ ጠቃሚነት በቃል ብቻ ሳይሆን በራሱ የግል ህይወትም ድንካን እየሰፋ ወንጌልን በመስበክ በተግባር ያስመከረ ታላቅ ሀዋርያ ነበር። የፕሮቴስታንት ሀይማኖትን ታሪክ ስናጠና ሀይማኖቱ ገና ከመነሻው ጠንካራ የስራ ባህልን እንደምነቱ አካል የሚወስድ፤ ተግቶ መስራት ለግለሰብ እና ለማህረሰብ ብልፅግና መሰረት ነው ብሎ የሚያምን ነው። የማህበረሰብ እና የታሪክ አጥኝወች በግልፅ እንዳስቀመጡት የአሜሪካ እና የአውሮፓ ብልፅግና ዋና ምክንያት የፕሮቴስታንት ሀይማኖት የሰራ ባህል ነው።
ይህ ሰባኪ እና መሰል የብልፅግና አስተማሪዎች የተገለጠውን የእግዚአብሄር ቃል እውነት በማጣመም የሀይማኖት አባቶች በህይወት ያሳዩንን ምሳሌ ችላ ብለው ሰራ አትስሩ ገንዘብ አምጡ በማለት ህዝቡን ግራ ያጋባሉ፤ ሰውን በቀቢፀ ተስፋም ይሞላሉ። ሰባኪው በሳይንስ ዙሪያ ሰለሚያስተምራቸወ ታላላቅ ግድፈቶች እና በጉባኤው ውስጥ ተቀምጠው ያዳምጡ ሰለነበሩ ሳይንቲስቶች አስተያየት በሚቀጥለው ፅሁፌ ለመፃፍ እሞክራለሁ።
“እውነትን ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችሁዋል”
እባካችሁ የእውነትን ወንጌል የሚሰብኩትን እንደግፍ!!

“ይሳካላችኋል ቤተክርስትያን” የክርስቶስ ህንጻ የትኛው ነው? ቤቱ ወይስ ምእመናው?

“ይሳካላችኋል ቤተክርስትያን” የክርስቶስ ህንጻ የትኛው ነው? ቤቱ ወይስ ምእመናው?
ysakalchuwal edited
ክፍል አንድ

“የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው።እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት።”
ኤፌ 1:17_23
“እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ጥልንም በመስቀሉ ገድሎ በእርሱ ሁለታቸውን በአንድ አካል ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ነው። መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና።እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም። በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፥ የማዕዘኑም ራስ ድንጋይ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው፤በእርሱም ሕንጻ ሁሉ እየተጋጠመ በጌታ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንዲሆን ያድጋል፤በእርሱም እናንተ ደግሞ ለእግዚአብሔር መኖሪያ ለመሆን በመንፈስ አብራችሁ ትሠራላችሁ።”
ኤፌ 2:14_22
83_100707_ds_ministermoneytn.jpg.CROP.original-original
በእነዚሀ የታመኑ የእግዚያብሔር ቃሎች መሰረት የእግዚያብሔር ህንጻ የቱ ነው? የሚታየው የቤቱ አካል ወይንስ ህዝበ ክርስቲያኑ? የእግዚያብሔር ቃል እንደሚያስተምረን እናም ብዙዎች አስተማሪዎች በተለያየ ግዜያቶች እንዳስተማሩት ይህ ከለይ ያሉት የመጽሀፍ ቅዱሳችን የእግዚያብሔር ቃሎች በትክክል የሚናገሩት ስለ ምእመናው የመንፈሳዊ ህይወት ጉዞ ማለትም ያለን መንፈሳዊ ህበረት : ከእግዚያብሔር ጋር ያለን ግኑኝነት : እርስ በእርስ ያለን ህብረት : እርስ በእርስ ያለን ፍቅር : የአምልኮአችን ሁኔታ : የእምነት ጽናታችንና የእምነት እድገታችን የሚታይበት የእምነት መሰራታችን በማይታየው በዋናው የህንጻ መሰረት ላይ ሲሆን የህንጻው ውጨኛው አካል ደግሞ ያመንበትንና የተማርነውን እምነት ሁሉም የሚያየውን የቅድስና ህይወታችንና የየእለት እንቅስቃሴያችን ማሳያ መስታወት ነው የውጨኛው አካላችን:: አለማውያን ቤት ሲሰሩ እንኳ በጣም የሚጠነቀቁትና ብዙ ገንዘብ የሚያወጡት ብዙ ግዜም የሚፈጅባቸው የሚሰሩት ቤት ውጨኛው አካል ላይ ሳይሆን መሰረቱ ላይ ነው መሰረቱ በደንብ ያልተሰራ ቤት አንድ ቀን መፍረሱ አይቀርም ሲፈርስ ደግሞ በህይወትና በንብረት ላይም ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል ከዚያም ባለፈ የስለ ልቦና ቀውሱም ያን ያህል ነው ለቤቱ ባለቤት ይህ በእንዲህ ሆኖ እንዳለ ወደ እኛ የዚህ ዘመን የክርስቶስ ህንጻ ስንመለስ የህንጻው መሀንዲሶች የሆኑት ነብያትና ሐዋርያት ቀየሰው የሰጡዋቸውን ፕላን የአሁኖቹ ግንበኞች ከፈረሱ ጋሪውን በማስቀደም ወይም ጌታ ኢየሱስ ለፈሪሳውያኖች እንዳለው የጽዋውን የወጪቱን ውጨኛውን ክፍል በማጥራት ላይ ይገኛሉ:: በአሁን ግዜ አንዳንድ ቤተክርስቲያን ስትሄዱ የህንጻ ግንባታ በየቦታው ጦፏል ህዝበ ክርስትያኑ ኑሮ አንገሽግሾት እራሱን ሊያረጋጋ እርሙን ቤተክርስቲያን ቢመጣ እነደ አምልኮ በመጀመሪያ የሚቀርብለት ያው ቤተክርስቲያኗ መሬት ገዝታ አሁን ደግሞ የህንጻ ማሰሪያ አንጡ ይባላል:: የት እንደገባ የማይታወቅ ምስኪን ክርስቲያን አሁን አሁን ለገንዘብ በባትሪ ይፈለጋል ምክንያቱም ህንጻ ተጀምሮዋላ የሚፈለገው ገንዘቡ ነው:: እንጂ ክርስቲያኑ አይደለም “የትም ፍጭው ዱቄቱን አምጭው” ይባል የለ ደግሞ በቤቱ ብቻ አያበቃም ዲኮር መደረግ አለበት ይባላል የውስጥ የማስጌጥ ሌላ ስራ ሌላ ልመና ሌላ ሮሮ እንደገና ይህም ያልቅና ዘመናይ መብራት ልክ እንደምሽት ክበብ ይግባ ይባላል እንደገና ሌላ ልመና ጣጣ ይህም እንደምንም ያልፍና የሙዚቃ መሳሪያ : የድምጽ ሲስተም : መብራት እየጠፋ ነው በሚል ጀነሬተር በቃ ይህ የመጨረሻ ነው ይባላል ይሄም እንደምንም ይፈጸማል ምእመናው ኡፈይ አለቀ ብሎ ሳይተነፍስ ቅርንጫፍ አጥቢያ ይባላል ይሄን ግዜ አብዛኛው ሞቅ ባለ የበረከት ቃል

“ይሳካልሀል/ሻል : ይከናወንልሀል/ሻል : ትበለጽጋለህ/ለሽ : በትዳር በልጅ በስራ በትምህርት ትባረካለህ/ለሽ” በሚል ስጋዊ ቅስቀሳ የገባ ስለሆነ ኢየሱስ ይሰጥሀል ብለውኝ ያለኝን ወሰዱብኝ በማለት ያጉረመርማል ከዚያም ከነ አንካቴው ክርስትና ይህ ነው እንዴ ብሎ የለየለት የአለም አለመኛ ይሆናል እከሌ ተመልሶ ባሰበት ይባላል እዛው በተጠመቀበት ቤተክርስትያን ማንም የሚፈልገው የለም እንደውም በተክርስቲያኗ ታወግዘዋለች ነገር ግን እረኞቹ አይናቸው አልበራም ይህ በቤታክርስቲ\ያን ምሬት የጠፋው ክርስትያን የከበረ የደም ዋጋ ስላለበት ጌታ ጠብቆት ወደ ቤቱ ይመልሰዋል እራሳቸውን እረኛ አድርገው የሾሙት እረኞች መንጋውን በትነው አሸሼ አግዳሜውን ያስነኩታል አንዳንዴ እነዚህን የእኛን ፓስተር ይሳካሎች የህዋ ምስክር ቄስ ነው የሚመስሉኝ ምክንያቱም የሚያስተምሩን ከአለም እንድንለይ ሳይሆን አለምን እንድናመልክ እንደ ጆቫ ምስክሮች ምድር ገነት ላይ እያስባሉን በአሁኑ ግዜ ይገኛሉ:: ለነገሩ የመጨረሻ ሰአት ስለሆነ እንዲህ አይነት ነገር እንዲከሰት የእግዚያብሔር ቃል ስለሚናገር
sin_724_482_80
“ስለ ክፉ ምኞት በዓለም ካለው ጥፋት አምልጣችሁ ከመለኮት ባሕርይ ተካፋዮች በተስፋ ቃል እንድትሆኑ፥ በእነዚያ ክብርና በጎነት የተከበረና እጅግ ታላቅ የሆነ ተስፋን ሰጠን። ስለዚህም ምክንያት ትጋትን ሁሉ እያሳያችሁ በእምነታችሁ በጎነትን ጨምሩ፥ በበጎነትም እውቀትን፥ በእውቀትም ራስን መግዛት፥ ራስንም በመግዛት መጽናትን፥ በመጽናትም እግዚአብሔርን መምሰል፥ እግዚአብሔርንም በመምሰል የወንድማማችን መዋደድ፥ በወንድማማችም መዋደድ ፍቅርን ጨምሩ።እነዚህ ነገሮች ለእናንተ ሆነው ቢበዙ፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ሥራ ፈቶችና ፍሬ ቢሶች እንዳትሆኑ ያደርጉአችኋልና፤ እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል።”
ቃሉን ለሚያቅ አይደንቅም ነገር ግን በጌታ ቃል ቅንአት በድፍረት እንናገራለን እንገስጻለን ምክንያቱም ማንም ዳግም ውልደት ባገኘ ክርስትያን ላይ የጌታ ፍርድ እንዲፈረድ ስለማንፈልግ ጌታ ግን ሊፈርድ በደጅ ነው ያለው:: እባካችሁ ታላቁ መጸሐፋችን ስለናንተ ስጋውያን አለመኛ ራሳቸውን በራሳቸው ስለሾሙ እረኞች እንዲህ ይላል::
“የእስራኤልም አምላክ የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። በመካከላችሁ ያሉት ነቢያቶቻችሁና ምዋርተኞቻችሁ አያታልሉአችሁ፥ እናንተም የምታልሙትን ሕልም አትስሙ። በስሜ ሐሰተኛ ትንቢትን ይናገሩላችኋልና፤ እኔም አልላክኋቸውም። እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና። ሰባው ዓመት በባቢሎን በተፈጸመ ጊዜ እጐበኛችኋለሁ፥ ወደዚህም ስፍራ እመልሳችሁ ዘንድ መልካሚቱን ቃሌን እፈጽምላችኋለሁ። ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። እናንተም ትጠሩኛለችሁ፥ ሄዳችሁም ወደ እኔ ትጸልያላችሁ፥ እኔም እሰማችኋለሁ።እናንተ ትሹኛላችሁ፥ በፍጹም ልባችሁም ከሻችሁኝ ታገኙኛላችሁ።”
ኤር 29:8_13”
snake
“ብዙ እረኞች የወይኑን ቦታዬን አጥፍተዋል፥ እድል ፈንታዬንም ረግጠዋል፤ የአምሮቴን እድል ፈንታ ምድረ በዳ አድርገውታል።”
ኤር 12:1o
“ይህን ከዚህ ውሰዱ፤ የአባቴን ቤት የንግድ ቤት አታድርጉት አላቸው።”
ጌታ ኢየሱስ
“ዳሩ ግን ባለ ጠጎች ሊሆኑ የሚፈልጉ በጥፋትና በመፍረስ ሰዎችን በሚያሰጥምና በሚያሰንፍ በሚጎዳም በብዙ ምኞትና በፈተና በወጥመድም ይወድቃሉ።”
1 ጢሞ 6:10
1aalove of money 971164_501034516638158_892926636_n
“ገንዘብን መውደድ የክፋት ሁሉ ሥር ነውና፥ አንዳንዶች ይህን ሲመኙ፥ ከሃይማኖት ተሳስተው በብዙ ሥቃይ ራሳቸውን ወጉ።”
1 ጢሞ 6:11
feature_mormon29__01__630x420
“እስከ መቼ በሰው ላይ ትቆማላችሁ? እናንተ ሁላችሁ እንዳዘነበለ ግድግዳ እንደ ፈረሰም ቅጥር ትገድላላችሁ።”
መዝ 61:3
“ነገር ግን ክብሬን ይሽሩ ዘንድ መከሩ፥ ሐሰትንም ይወድዳሉ፤ በአፋቸው ይባርካሉ፥ በልባቸውም ይረግማሉ።”

“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንና ምእመና ዘንድ ገድለ ተአምረኛነታቸውና ፈዋሽነታቸው የሚነገርላቸው የመምህር ግርማ ወንድሙ ፈውስና ተአምር በመጽሐፍ ቅዱስ ዕይታ”


“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያንና ምእመና ዘንድ ገድለ ተአምረኛነታቸውና ፈዋሽነታቸው የሚነገርላቸው የመምህር ግርማ ወንድሙ ፈውስና ተአምር በመጽሐፍ ቅዱስ ዕይታ”
“በመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ያለ ፈውስና ተአምራት በሙሉ የፈውስና የተአምራት ምንጩ ዲያብሎስ ነው::!”
hqdefault
images_priest_322394505
memhir9
የአለም (ዲያብሎስ) መፈክር “ማየት ማመን ነው” የእግዚያብሔር መፈክር ደግሞ “ማመን ማየት ነው” የሚሉን ሲሆን ጌታ ኢየሱስም “ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው::”
እኔ በበኩሌ በቅርብ ግዜ ከመምህር ግርማ ታላላቅ ተአምራትንና አስደናቂ የአጋንንትን ጫወታዎችን እንደማይ ተስፋ አደርጋለሁ::
“በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና። በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና።”
“ በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
ዮሐ 10:9_11
“ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
“ ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።” ዮሐ 20:29_31
“ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።” 1ዮሐንስ ምዕራፍ 4
“ ወንድሞች ሆይ፥ እናንተ የተማራችሁትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና ማሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንድትመለከቱ እለምናችኋለሁ፥ ከእነርሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ፤እንዲህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና፥ በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ልብ ያታልላሉ።” ሮሜ 16:17_18
“ የላከኝ አብም እርሱ ስለ እኔ መስክሮአል። ድምፁን ከቶ አልሰማችሁም፥ መልኩንም አላያችሁም፤እርሱም የላከውን እናንተ አታምኑምና በእናንተ ዘንድ የሚኖር ቃሉ የላችሁም።እናንተ በመጻሕፍት የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ይመስላችኋልና እነርሱን ትመረምራላችሁ፤ እነርሱም ስለ እኔ የሚመሰክሩ ናቸው፤ነገር ግን ሕይወት እንዲሆንላችሁ ወደ እኔ ልትመጡ አትወዱም። ከሰው ክብርን አልቀበልም፤ ዳሩ ግን የእግዚአብሔር ፍቅር በራሳችሁ እንደ ሌላችሁ አውቃችኋለሁ።እኔ በአባቴ ስም መጥቻለሁ አልተቀበላችሁኝምም፤ ሌላው በራሱ ስም ቢመጣ እርሱን ትቀበሉታላችሁ።እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትቀባበሉ ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ?እኔ በአብ ዘንድ የምከሳችሁ አይምሰላችሁ፤ የሚከሳችሁ አለ፤ እርሱም ተስፋ የምታደርጉት ሙሴ ነው።ሙሴንስ ብታምኑት እኔን ባመናችሁ ነበር፤ እርሱ ስለ እኔ ጽፎአልና።መጻሕፍትን ካላመናችሁ ግን ቃሌን እንዴት ታምናላችሁ?” ዮሐ 5:37_47
ከላይ ለመግቢያ ከዮሐንስ ወንጌል የወሰድኩትን ጌታ ኢየሱስ ያደረገውን ተአምርና ፈውስ ዋና አላማው ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያን ግዜ ለሐዋሪያቶች እንዲታመን የፈለገው ባደረገውና ባሳያቸው ተአምራት እንዲያምኑ ሳይሆን ማመን ያለባቸው እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚያብሔር ልጅ እንደሆነ እንዲያምኑ የሰራው ተአምርና ፈውስ ነው:: ለዚህ ነው ብዙ ግዜ ጌታ ኢየሱስ ከፈወሳቸው ቡኋላ ሁሌም የሚላቸው አንድ ቃል አለ እሱም “አንተ ሰው እምነትህ አድኖሀል” አንቺ ሴት እምነትሽ አድኖሻል” የቱ እምነት ነው ያዳናቸው ከተባለ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚያብሔር ልጅ መሆኑን በስጋ እንደመጣ እንደተሰቀለ : እንደሞተ : እንደተቀበረ : በሶስተኛውም ቀን ሞትን ድል አድርጎ እግዚያብሔር እንዳስነሳው : እንደአረገ : ተመልሶም እንደሚመጣ : ከሞት እንደሚያስናሳና እንደሚገዛ :: ይህ ትክክለኛውና ዋናው የክርስትያን እምነት ነው:: በእነዚህ እምነት ውስጥ ጥበብ : እውቀት : ማስተዋል : ሰላም : ፈውስ : ብልጥግና : ስኬትና መከናወን ሌሎቹም ነገሮች አሉ እንጂ እግዚያብሔር ከበሽታ ለመዳን : ለብልጥግና : ለስኬት አይታመንም እግዚያብሔር የሚታመነው ለዘላለም ህይወት ነው:: ነገር ግን ዮሐንስ ወንጌሉን ለምን እንደጻፈው ሲናገር “ ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።” ዮሐ 20:29_31
በክርስቶስ ኢየሱስ የዳግም ውልደትን ያገኘ ክርስቲያን ሁሉ በየትኛውም ተአምራት ማመን የለብንም ምክንያቱም ዲያብሎስ አንዱና ዋና ማሳሳቻው ከተራ ጥንቆላና መተት እስከ ሰማይ ድንቅ ተአምራት ማሳየት ችሎታ እንዳለው ወንጌላችን በብዙ ቦታ ይገልጸዋል ለእዚህም ነው የአለም (ዲያብሎስ) መፈክር “ማየት ማመን ነው” የእግዚያብሔር መፈክር ደግሞ “እመንና እይ” የሚሉን ጌታ ኢየሱስም “ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው::” የሚለን ብዙ ግዜ ስለ እምነት ሲነሳ በክርስትና እምነት ውስጥ መጠየቅ ያለበት አንድ ወሳኝ ጥያቄ አለ እርሱም እምነት ምንድ ነው? የሚለውን ሁሉም ክርስትያን ማወቅ ያለበት ቁልፍ ጥያቄ ነው እምነት ብዙ ሰዎች እምነትንና ሀይማኖትን ለይተው ማወቅ ተስኗቸዋል:: በይበልጥ እንደ ኦርቶዶክስ የሐይማኖት እምነት ተከታዮች ያልዳኑ ቤተሰቦቻችን የሐይማኖት እምነት እይታ በእነርሱ የሐይማኖት እምነት ውስጥ ሌላው ቢቀር የሚቀባ የእምነት አፈርና አመድ ሁሉ እምነት ነው:: በድቅድቅ የጨለማ እምነት ውስጥ በነበርንበት ግዜ ሁላችንም ይህንን የድቅድቅ ጨለማ የእምነት አፈርና አመድ ግንባራችንን መስቀል ሰርተን ተለቅልቀናል ዛሬ ምስጋና ለብርሀን ጌታ ለእግዚያብሔር ልጅ ለናዝሬቱ ለኢየሱስ ክርስቶስ ይግባውና ከድቅድቅ ጨለማ ወደሚደነቅ ብርሀን ስቦ አወጣን እኔ በበኩሌ ያንን የድቅድቅ ጨለማ ዘመን ሳስበው የነበረውና ያሳለፍኩት ህይወቴ ይዘገንነኛል :: እምነት ምንድ ነው? የሚለውን እስኪ ወንጌል ይመልሰው::
“እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ፥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው።ለሽማግሌዎች የተመሰከረላቸው በዚህ ነውና።ዓለሞች በእግዚአብሔር ቃል እንደ ተዘጋጁ፥ ስለዚህም የሚታየው ነገር ከሚታዩት እንዳልሆነ በእምነት እናስተውላለን።አቤል ከቃየል ይልቅ የሚበልጥን መሥዋዕት ለእግዚአብሔር በእምነት አቀረበ፥ በዚህም፥ እግዚአብሔር ስለ ስጦታው ሲመሰክር፥ እርሱ ጻድቅ እንደ ሆነ ተመሰከረለት፤ ሞቶም ሳለ በመሥዋዕቱ እስከ አሁን ይናገራል።ሄኖክ ሞትን እንዳያይ በእምነት ተወሰደ፥ እግዚአብሔርም ስለ ወሰደው አልተገኘም። ሳይወሰድ እግዚአብሔርን ደስ እንዳሰኘ ተመስክሮለታልና፤ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ኖኅ ገና ስለማይታየው ነገር ተረድቶ እግዚአብሔርን እየፈራ ቤተ ስዎቹን ለማዳን መርከብን በእምነት አዘጋጀ፥ በዚህም ዓለምን ኰነነ፥ በእምነትም የሚገኘውን ጽድቅ ወራሽ ሆነ።አብርሃም የተባለው ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ስፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፥ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ።ለእንግዶች እንደሚሆን በተስፋ ቃል በተሰጠው አገር በድንኳን ኖሮ፥ ያን የተስፋ ቃል አብረውት ከሚወርሱ ከይስሐቅና ከያዕቆብ ጋር፥ እንደ መጻተኛ በእምነት ተቀመጠ፤መሠረት ያላትን፥ እግዚአብሔር የሠራትንና የፈጠራትን ከተማ ይጠብቅ ነበርና።ተስፋ የሰጠው የታመነ እንደ ሆነ ስለ ቈጠረች፥ ሣራ ራስዋ ደግሞ ዕድሜዋ እንኳ ካለፈ በኋላ ዘርን ለመፅነስ ኃይልን በእምነት አገኘች።ስለዚህ ደግሞ በብዛታቸው እንደ ሰማይ ኮከብ እንደማይቈጠርም በባሕር ዳር እንዳለ አሸዋ የነበሩት የሞተን ሰው እንኳ ከመሰለው ከአንዱ ተወለዱ።እነዚህ ሁሉ አምነው ሞቱ፥ የተሰጣቸውን የተስፋ ቃል አላገኙምና፤ ዳሩ ግን ከሩቅ ሆነው አዩትና ተሳለሙት፥ በምድሪቱም እንግዶችና መጻተኞች እንዲሆኑ ታመኑ።እንዲህ የሚሉት ለእነርሱ የሚሆነውን አገር እንዲፈልጉ ያመለክታሉና።ያን የወጡበትን አገር አስበው ቢሆኑ፥ ሊመለሱ ጊዜ በሆነላቸው ነበር፤አሁን ግን የሚበልጠውን እርሱም ሰማያዊ አገር ይናፍቃሉ። ስለዚህ እግዚአብሔር አምላካቸው ተብሎ ሊጠራ በእነርሱ አያፍርም፥ ከተማን አዘጋጅቶላቸዋልና።አብርሃም በተፈተነበት ጊዜ ይስሐቅን በእምነት አቀረበ፥ የተስፋን ቃል የተቀበለው። በይስሐቅ ዘር ይጠራልሃል የተባለለት እርሱም አንድ ልጁን አቀረበ፤እግዚአብሔር ከሙታን እንኳ ሊያስነሣው እንዲቻለው አስቦአልና፥ ከዚያም ደግሞ በምሳሌ አገኘው።ይስሐቅ ሊመጣ ስላለው ነገር ያዕቆብንና ዔሳውን በእምነት ባረካቸው።ያዕቆብ ሲሞት በእምነት የዮሴፍን ልጆች እያንዳንዳቸው ባረካቸው፥ በዘንጉም ጫፍ ተጠግቶ ሰገደ።ዮሴፍ ወደ ሞት ቀርቦ ሳለ በእምነት ስለ እስራኤል ልጆች መውጣት አስታወሰ፥ ስለ አጥንቱም አዘዛቸው። ሙሴ ከተወለደ በኋላ ወላጆቹ ያማረ ሕፃን መሆኑን አይተው በእምነት ሦስት ወር ሸሸጉት የንጉሥንም አዋጅ አልፈሩም።ሙሴ ካደገ በኋላ የፈርዖን የልጅ ልጅ እንዳይባል በእምነት እምቢ አለ፤ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና።የንጉሡን ቍጣ ሳይፈራ የግብፅን አገር የተወ በእምነት ነበር፤ የማይታየውን እንደሚያየው አድርጎ ጸንቶአልና።አጥፊው የበኵሮችን ልጆች እንዳይነካ ፋሲካንና ደምን መርጨትን በእምነት አደረገ።በደረቅ ምድር እንደሚያልፉ በኤርትራ ባሕር በእምነት ተሻገሩ፥ የግብፅ ሰዎች ግን ሲሞክሩ ተዋጡ።የኢያሪኮ ቅጥር ሰባት ቀን ከዞሩበት በኋላ በእምነት ወደቀ።ጋለሞታይቱ ረዓብ ሰላዮችን በሰላም ስለ ተቀበለቻቸው ከማይታዘዙ ጋር በእምነት አልጠፋችም።እንግዲህ ምን እላለሁ? ስለ ጌዴዎንና ስለ ባርቅ ስለ ሶምሶንም ስለ ዮፍታሔም ስለ ዳዊትና ስለ ሳሙኤልም ስለ ነቢያትም እንዳልተርክ ጊዜ ያጥርብኛልና።እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሡ፥ ጽድቅን አደረጉ፥ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አገኙ፥የአንበሶችን አፍ ዘጉ፥ የእሳትን ኃይል አጠፉ፥ ከሰይፍ ስለት አመለጡ፥ ከድካማቸው በረቱ፥ በጦርነት ኃይለኞች ሆኑ፥ የባዕድ ጭፍሮችን አባረሩ።ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤ሌሎችም መዘበቻ በመሆንና በመገረፍ ከዚህም በላይ በእስራትና በወኅኒ ተፈተኑ፤በድንጋይ ተወግረው ሞቱ፥ ተፈተኑ፥ በመጋዝ ተሰነጠቁ፥ በሰይፍ ተገድለው ሞቱ፥ ሁሉን እያጡ መከራን እየተቀበሉ እየተጨነቁ የበግና የፍየል ሌጦ ለብሰው ዞሩ፤ዓለም አልተገባቸውምና በምድረ በዳና በተራራ፥ በዋሻና በምድር ጕድጓድ ተቅበዘበዙ።እነዚህም ሁሉ በእምነታቸው ተመስክሮላቸው ሳሉ የተሰጠውን የተስፋ ቃል አላገኙም፥ ያለ እኛ ፍጹማን እንዳይሆኑ እግዚአብሔር ስለ እኛ አንዳች የሚበልጥ ነገርን አስቀድሞ አይቶ ነበርና።” ዕብ 11
የዛሬው ጽሁፌ የሚያተኩረው በተአምር የእምነት ፈውሶች ላይ ይሆናል ለዚህም ደግሞ ብዙ ተከታይ ምእመና ያሉዋት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የተአምረ ፈውስ ሰጪ የሆኑትና በምእመናው ዘንድ እንደ ተአምረ ነቢይ የሚታዪት ታዋቂው መምህር ግርማ የተባሉ የኦርቶዶክስ ሀይማኖት የእምነተ – ጣኦት ተአምረ ፈዋሽ በምእመናቸውና በጣኦት አምላኪዎችና አድናቂዎች ዘንድ ይመለካሉ ያስመልካሉ ይወደሳሉ…. ሌላም ሌላም ይባልላቸዋል::

ሁሉም ማለት ይቻላል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምእመና በእነ መምህር ግርማ ተራ የሆነውን ተአምረ የአጋንንትን ወሬ እንደ አንድ መደበኛ የሐይማኖት የእምነት ትምህርት ባሉበት ሁኔታ ይማራሉ በየሶሻል ሚዲያው ሼር ያደርጋሉ ሌላም ሌላም የመምህር ግርማ የአጋንንት ወሬ ተአምር ዋና አላማው ህዝበ ክርስትያኑን አደንዝዞ ኦርቶዶክስ የሚባል የሐይማኖትን እምነት ማስመለክ ነው:: እኔ በግሌ ከኦርቶዶክሱ መምህር ግርማ በጣም ብዙ ታላላቅ ተአምር እጠብቃለሁ:: ምክንያቱም በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል አካባቢ ያሉ የኦርቶዶክስ ሐይማኖት እምነት ቄሶችና መሪጌታዎች ዘንድ ከመምህር ግርማ የሚበልጥ ትላላቅ ድንቅ ተአምራት ይሰራሉ በእዚያ አካባቢ ያሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ዘንድ ይህ በእግዚያብሔር ዘንድ ጸያፍ የሆነው የዲያብሎስ ስራ ድግምት : መተት : ጥንቆላ ልዩ ልዩ የሆኑ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ በደብተራዎችና በቄሶች የሚሰሩትን ጸያፍ ስራዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ተከታዮች ዘንድ እንደ ከእግዚያብሔር እንደተሰጠ ጥበብ ይቆጠራል:: በእዚህ ጉዳይ ብዙዎች የእምነቱ ተከታዮች በኩራት አፋቸውን ሞልተው “እግዚያብሔር ለሰው ልጆች ከሰጠው ጥበብ አንዱ ይህ ነው ብለው ያምናሉ::

እዚህ ላይ ድግምት : መተት : ጥንቆላ ልዩ ልዩ የሆኑ ተአምራቶች ስራዎች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስና ኢስላም ሀይማኖት ዘንድ በስፋት ይታወቃሉ የወር መባቻዎችን ሚኪያኤል : ገብርኤል : መድሀኒያለም : ልደታ ማርያምና ጊዮርጊስና ሌሎችም በሁለቱም ሀይማኖት አባቶች : በጦንቃዮችና በመተተኞች ዘንድ ትልቅ የሰይጣናዊ ስራ ተልእኮ ማስፈጸሚያ ተወዳጅ ቀኖች ናቸው:: ለዚህም ደግሞ ለፈውስና ተአምራት መስሪያ የተደገመባቸው መቁጠሪያ ጨሌዎች በሁለቱም የሀይማኖት እምነቶች ዋና የተአምር መስሪያና መፈወሻ ቁሳቁስ ናቸው:: ብዙ ግዜ ድግምተኞችና መተተኞች የኦርቶዶክስና የኢስላም ሀይማኖት ተከታዮች ናቸው:: እንዲሁም በእምነት ተቋማቸውና በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ፍርሀትና ክብር ይሰጣቸዋል:: እዚህ ላይ አንድ ምስክር አለ ይህ መስካሪ የቀድሞው በደሴ የሚገኙ አንድ በኢትዮጵያ የታወቁ አንድ ተአምረኛ ጦንቃይ ህዝብ ግንኙነት የነበረ ሰው ሲሆን እኝሁ ታዋቂ ጦንቃይ በግዜው ተአምራታቸው ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን አንስቶ እስከ ግል መገናኛ ብዙሀኖች ድረስ ሰፊ ዘገባ የተሰጣቸው የተከበሩ ተአምረኛ ጦንቃይ ነበሩ ስለእሳቸው ገድለ ተአምራታቸውን በግዜው የእሳቸው ህዝብ ግንኙነት የሆነው ፓስተር ተስፋዬ ገብሬ የቀድሞ የደሴው ታዋቂው ጦንቃይ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ምስክር እንዲህ በማለት የነበረውን ታላቅ የተአምራት ግዜ ይተርካል::



“ አምላክህ እግዚአብሔር ወደሚሰጥህ ምድር በገባህ ጊዜ እነዚያ አሕዛብ የሚያደርጉትን ርኵሰት ታደርግ ዘንድ አትማር። ወንድ ልጁን ሴት ልጁን በእሳት የሚያሳልፍ፥ ምዋርተኛም፥ ሞራ ገላጭም፥አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ። ይህንም የሚያደርግ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ነው፤ ስለዚህም ርኵሰት አምላክህ እግዚአብሔር ከፊትህ ያሳድዳቸዋል። አንተ ግን በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ ፍጹም ሁን::”
ዘዳ 18:9_13
የዚህ የእኔ መልእክት ዋና አላማ የፈውሱ ጤናማነት ላይ ያተኩራል:: ስለፈውስ ስናወራ አለማውያን እራሳቸው ሁለት አይነት የፈውስ ጥበብ አላቸው አንደኛው በሽታውን ከበሽተኛው ላንዴና ለመጨረሻ ግዜ ማስወገድ (ብዙ ግዜ የበሽታው መጥፎ ጠባሳ ተፈዋሹ ሰው ላይ የሚቀር ) ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ከበሽተኛው ጋር በሽታው እራሱ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ አብሮ የሚኖር ይሆናል ልክ እንደ ካንሰርና ኤች አይ ቪ ኤድስ በሽታ የመሳሰሉት ማለት ይሆናል::
ይህን ካልኩ ዘንዳ ወደ መንፈሳዊው የእምነት ፈውስ በሁለት ይከፈላሉ:: እነሱም የእግዚያብሔር መንፈሳዊው የእምነት ፈውስ እና የዲያብሎስ ሀይማኖታዊ የእምነት ፈውስ በመባል ይታወቃሉ:: የእግዚያብሔር መንፈሳዊ ፈውስ የሚገኘው ከላይ ለመግቢያ እንዳሳየሁት በእምነት ነው እምነቱም ከአጋንንት ጋር መጯጯህ : በሽታ መፈወስ : እሳት ከሰማይ ማውረድና ዝናብ ማዝነብ ምናምን ሳይሆን “እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚያብሔር ልጅ እንደሆነ እንዲያምኑ የሰራው ተአምርና ፈውስ ነው:: ለዚህ ነው ብዙ ግዜ ጌታ ኢየሱስ ከፈወሳቸው ቡኋላ ሁሌም የሚላቸው አንድ ነገር አለ እሱም “አንተ ሰው እምነትህ አድኖሀል” አንቺ ሴት እምነትሽ አድኖሻል” የቱ እምነት ነው ያዳናቸው ከተባለ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚያብሔር ልጅ መሆኑን በስጋ እንደመጣ እንደተሰቀለ : እንደሞተ : እንደተቀበረ : በሶስተኛውም ቀን ሞትን ድል አድርጎ እግዚያብሔር እንዳስነሳው : እንደአረገ : ተመልሶም እንደሚመጣ : ከሞት እንደሚያስናሳና እንደሚገዛ :: ማመን ነው ለዚህም ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በብዙ ቦታ ተጽፎ እናገኘዋለን እሱም እንደሚከተለው ይነበባል::
የእግዚያብሔር መንፈሳዊ ፈውስ
“ ስለ እነዚህም የመሰከረ ይህንንም ጽፎ ያለ ይህ ደቀ መዝሙር ነው፥ ምስክሩም እውነት እንደ ሆነ እናውቃለን።ኢየሱስም ያደረገው ብዙ ሌላ ነገር ደግሞ አለ፤ ሁሉ በእያንዳንዱ ቢጻፍ ለተጻፉት መጻሕፍት ዓለም ራሱ ባልበቃቸውም ይመስለኛል።”
ዮሐ 21:24:25
“ ኢየሱስም። ስለ አየኸኝ አምነሃል፤ ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው አለው። ኢየሱስም በዚህ መጽሐፍ ያልተጻፈ ሌላ ብዙ ምልክት በደቀ መዛሙርቱ ፊት አደረገ፤ነገር ግን ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ታምኑ ዘንድ፥ አምናችሁም በስሙ ሕይወት ይሆንላችሁ ዘንድ ይህ ተጽፎአል።” ዮሐ 20:29_31
“ ልባችሁ አይታወክ፤ በእግዚአብሔር እመኑ፥ በእኔም ደግሞ እመኑ።በአባቴ ቤት ብዙ መኖሪያ አለ፤ እንዲህስ ባይሆን ባልኋችሁ ነበር፤ ስፍራ አዘጋጅላችሁ ዘንድ እሄዳለሁና፤ሄጄም ስፍራ ባዘጋጅላችሁ፥ እኔ ባለሁበት እናንተ ደግሞ እንድትሆኑ ሁለተኛ እመጣለሁ ወደ እኔም እወስዳችኋለሁ። ወደምሄድበትም ታውቃላችሁ፥ መንገዱንም ታውቃላችሁ።ቶማስም። ጌታ ሆይ፥ ወደምትሄድበት አናውቅም፤ እንዴትስ መንገዱን እናውቃለን? አለው። ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። እኔንስ ብታውቁኝ አባቴን ደግሞ ባወቃችሁ ነበር። ከአሁንም ጀምራችሁ ታውቁታላችሁ አይታችሁትማል አለው። ፊልጶስ። ጌታ ሆይ፥ አብን አሳየንና ይበቃናል አለው።ኢየሱስም አለው። አንተ ፊልጶስ፥ ይህን ያህል ዘመን ከእናንተ ጋር ስኖር አታውቀኝምን? እኔን ያየ አብን አይቶአል፤ እንዴትስ አንተ። አብን አሳየን ትላለህ? እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ አታምንምን? እኔ የምነግራችሁን ቃል ከራሴ አልናገረውም፤ ነገር ግን በእኔ የሚኖረው አብ እርሱ ሥራውን ይሠራል። እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ፤ ባይሆንስ ስለ ራሱ ስለ ሥራው እመኑኝ። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ እርሱ ደግሞ ያደርጋል፤ ከዚህም የሚበልጥ ያደርጋል፥እኔ ወደ አብ እሄዳለሁና፤ አብም ስለ ወልድ እንዲከበር በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ አደርገዋለሁ።ማናቸውንም ነገር በስሜ ብትለምኑ እኔ አደርገዋለሁ።ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ። እኔም አብን እለምናለሁ ለዘላለምም ከእናንተ ጋር እንዲኖር ሌላ አጽናኝ ይሰጣችኋል፤ እርሱም ዓለም የማያየውና የማያውቀው ስለ ሆነ ሊቀበለው የማይቻለው የእውነት መንፈስ ነው፤ ነገር ግን ከእናንተ ዘንድ ስለሚኖር በውሥጣችሁም ስለሚሆን እናንተ ታውቃላችሁ። ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ገና ጥቂት ዘመን አለ ከዚህም በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና እናንተ ደግሞ ሕያዋን ትሆናላችሁ። እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ።ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ። የአስቆሮቱ ያይደለ ይሁዳ። ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው? አለው። ኢየሱስም መለሰ አለውም። የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም።ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል።ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።እኔ እሄዳለሁ ወደ እናንተም እመጣለሁ እንዳልኋችሁ ሰማችሁ። የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።ከሆነም በኋላ ታምኑ ዘንድ አሁን አስቀድሞ ሳይሆን። ነግሬአችኋለሁ።ከእንግዲህ ወዲህ ከእናንተ ጋር ብዙ አልናገርም፥ የዚህ ዓለም ገዥ ይመጣልና፤ በእኔ ላይም አንዳች የለውም፤ነገር ግን አብን እንድወድ ዓለም ሊያውቅ፥ አብም እንዳዘዘኝ፥ እንዲሁ አደርጋለሁ። ተነሡ፤ ከዚህ እንሂድ።”
ዮሐ 14
“ በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማሪያም ያገኛል። ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ።መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።”
ዮሐ 10:9_11
“ በመሸም ጊዜ አጋንንት ያደረባቸውን ብዙዎችን ወደ እርሱ አመጡ፤ በነቢዩ በኢሳይያስ። እርሱ ድካማችንን ተቀበለ ደዌያችንንም ተሸከመ የተባለው ይፈጸም ዘንድ፥ መናፍስትን በቃሉ አወጣ፥ የታመሙትንም ሁሉ ፈወሰ። ”
ማቴ 8:16_17
“ እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤በልብዋ። ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ ትል ነበረችና።ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና። ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች።”
ማቴ 9:20_22
“ ኢየሱስም መልሶ። ምን ላደርግልህ ትወዳለህ? አለው። ዕውሩም። መምህር ሆይ፥ አይ ዘንድ አለው። ኢየሱስም። ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው። ወዲያውም አየ በመንገድም ተከተለው።”
ማር 10:51_52
“ እነርሱም እየጮኹ። ኢየሱስ ሆይ፥ አቤቱ፥ ማረን አሉ። አይቶም። ሂዱ፥ ራሳችሁን ለካህናት አሳዩ አላቸው። እነሆም፥ ሲሄዱ ነጹ። ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፥እያመሰገነውም በእግሩ ፊት በግንባሩ ወደቀ፤ እርሱም ሳምራዊ ነበረ። ኢየሱስም መልሶ። አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ? ከዚህ ከልዩ ወገን በቀር እግዚአብሔርን ሊያከብሩ የተመለሱ አልተገኙም አለ።እርሱንም። ተነሣና ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው።”
ሉቃ 17:13_19
“ እርሱም ገና ሲናገር ከምኵራብ አለቃው ቤት ዘንድ የመጡት። ልጅህ ሞታለች፤ ስለ ምን መምህሩን አሁን ታደክመዋለህ? አሉት። ኢየሱስ ግን የተናገሩትን ቃል አድምጦ ለምኵራቡ አለቃ። እመን ብቻ እንጂ አትፍራ አለው። ከጴጥሮስም ከያዕቆብም ከያዕቆብም ወንድም ከዮሐንስ በቀር ማንም እንዲከተለው አልፈቀደም።ወደ ምኵራቡ አለቃ ቤትም መጥቶ ሰዎች ሲንጫጩና ሲያለቅሱ ዋይታም ሲያበዙ አየ፤ገብቶም። ስለ ምን ትንጫጫላችሁ ታለቅሳላችሁም? ብላቴናይቱ ተኝታለች እንጂ አልሞተችም አላቸው።በጣምም ሳቁበት። እርሱ ግን ሁሉን አስወጥቶ የብላቴናይቱን አባትና እናትም ከእርሱ ጋር የነበሩትንም ይዞ ብላቴናይቱ ወዳለችበት ገባ። የብላቴናይቱንም እጅ ይዞ። ጣሊታ ቁሚ አላት፤ ፍችውም አንቺ ብላቴና ተነሽ እልሻለሁ ነው።ብላቴናይቱም የአሥራ ሁለት ዓመት ልጅ ነበረችና ወዲያው ቆማ ተመላለሰች። ወዲያውም ታላቅ መገረም ተገረሙ።”
ማር 5:35_42
“ ኢየሱስ። ድንጋዩን አንሡ አለ። የሞተውም እኅት ማርታ። ጌታ ሆይ፥ ከሞተ አራት ቀን ሆኖታልና አሁን ይሸታል አለችው። ኢየሱስ። ብታምኚስ የእግዚአብሔርን ክብር እንድታዪ አልነገርሁሽምን? አላት።ድንጋዩንም አነሡት። ኢየሱስም ዓይኖቹን ወደ ላይ አንሥቶ። አባት ሆይ፥ ስለ ሰማኸኝ አመሰግንሃለሁ።ሁልጊዜም እንድትሰማኝ አወቅሁ፤ ነገር ግን አንተ እንደ ላክኸኝ ያምኑ ዘንድ በዚህ ዙሪያ ስለ ቆሙት ሕዝብ ተናገርሁ አለ። ይህንም ብሎ በታላቅ ድምፅ። አልዓዛር ሆይ፥ ወደ ውጭ ና ብሎ ጮኸ። የሞተውም እጆቹና እግሮቹ በመግነዝ እንደ ተገነዙ ወጣ፤ ፈቱም በጨርቅ እንደ ተጠመጠመ ነበር። ኢየሱስም። ፍቱትና ይሂድ ተዉት አላቸው። ስለዚህ ወደ ማርያም ከመጡት፥ ኢየሱስም ያደረገውን ካዩት ከአይሁድ ብዙዎች በእርሱ አመኑ:: ”
ዮሐ 11:39_45
“ ከእናንተ የታመመ ማንም ቢኖር የቤተ ክርስቲያንን ሽምግሌዎች ወደ እርሱ ይጥራ፤ በጌታም ስም እርሱን ዘይት ቀብተው ይጸልዩለት። የእምነትም ጸሎት ድውዩን ያድናል ጌታም ያስነሣዋል፤ ኃጢአትንም ሠርቶ እንደ ሆነ ይሰረይለታል።እርስ በርሳችሁ በኃጢአታችሁ ተናዘዙ። ትፈወሱም ዘንድ እያንዳንዱ ስለ ሌላው ይጸልይ፤ የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች።ኤልያስ እንደ እኛ የሆነ ሰው ነበረ፥ ዝናብም እንዳይዘንብ አጥብቆ ጸለየ፥ በምድርም ላይ ሦስት ዓመት ከስድስት ወር አልዘነበም፤ ሁለተኛም ጸለየ፥ሰማዩም ዝናብን ሰጠ ምድሪቱም ፍሬዋን አበቀለች። ወንድሞቼ ሆይ፥ ከእናንተ ማንም ከእውነት ቢስት አንዱም ቢመልሰው፥ኃጢአተኛን ከተሳሳተበት መንገድ የሚመልሰው ነፍሱን ከሞት እንዲያድን፥ የኃጢአትንም ብዛት እንዲሸፍን ይወቅ።”
ያቆ 5:14_20
“ ከእናንተ ግን ማንም ጥበብ ቢጎድለው፥ ሳይነቅፍ በልግስና ለሁሉ የሚሰጠውን እግዚአብሔርን ይለምን፥ ለእርሱም ይሰጠዋል።ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። የተዋረደው ወንድም ግን በከፍታው፥ ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ያልፋልና።ፀሐይ ከትኵሳት ጋር ይወጣልና፥ ሣርንም ያጠወልጋልና፥ አበባውም ይረግፋልና፥ የመልኩም ውበት ይጠፋልና፤ እንዲሁ ደግሞ ባለ ጠጋው በመንገዱ ይዝላል። በፈተና የሚጸና ሰው የተባረከ ነው፤ ከተፈተነ በኋላ ለሚወዱት ተስፋ ስለ እርሱ የሰጣቸውን የሕይወትን አክሊል ይቀበላልና።ማንም ሲፈተን። በእግዚአብሔር እፈተናለሁ አይበል፤ እግዚአብሔር በክፉ አይፈተንምና፤ እርሱ ራሱስ ማንንም አይፈትንም።ነገር ግን እያንዳንዱ በራሱ ምኞት ሲሳብና ሲታለል ይፈተናል።ከዚህ በኋላ ምኞት ፀንሳ ኃጢአትን ትወልዳለች፤ ኃጢአትም ካደገች በኋላ ሞትን ትወልዳለች።የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ።በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ።”
ያቆ 1:5_17
“ እነርሱም ሲወጡ እነሆ፥ ጋኔን ያደረበትን ዲዳ ሰው ወደ እርሱ አመጡ። ጋኔኑንም ካወጣው በኋላ ዲዳው ተናገረ። ሕዝቡም። እንዲህ ያለ በእስራኤል ዘንድ ከቶ አልታየም እያሉ ተደነቁ። ፈሪሳውያን ግን። በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል አሉ።”
ማቴ 9:32_34
“ ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና።ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው። ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ። ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ።ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት። ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም። ይህ ዓይነት ግን ከጸሎትና ከጦም በቀር አይወጣም አላቸው።”
ማቴ 17:14_21
“ ከማይቀበላችሁም ቃላችሁንም ከማይሰሙ ሁሉ፥ ከዚያ ቤት ወይም ከዚያች ከተማ ስትወጡ የእግራችሁን ትቢያ አራግፉ። እውነት እላችኋለሁ፥ በፍርድ ቀን ከዚያች ከተማ ይልቅ ለሰዶምና ለገሞራ አገር ይቀልላቸዋል።”
ማቴ 10:14_15
ኢሳያስ 53።
“ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር። እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈከደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል። ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሰከማል። ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።”
“ እነሆም፥ ከአሥራ ሁለት ዓመት ጀምሮ ደም የሚፈስሳት ሴት በኋላው ቀርባ የልብሱን ጫፍ ዳሰሰች፤ በልብዋ። ልብሱን ብቻ የዳሰስሁ እንደ ሆነ፥ እድናለሁ ትል ነበረችና።ኢየሱስም ዘወር ብሎ አያትና። ልጄ ሆይ፥ አይዞሽ፤ እምነትሽ አድኖሻል አላት። ሴቲቱም ከዚያች ሰዓት ጀምራ ዳነች።”
ማቴ 9:20_22
“ ወደ ሕዝቡም ሲደርሱ አንድ ሰው ወደ እርሱ ቀረበና ተንበርክኮ። ጌታ ሆይ፥ ልጄን ማርልኝ፥ በጨረቃ እየተነሣበት ክፉኛ ይሣቀያልና፤ብዙ ጊዜ በእሳት ብዙ ጊዜም በውኃ ይወድቃልና። ወደ ደቀ መዛሙርትህም አመጣሁት ሊፈውሱትም አቃታቸው አለው። ኢየሱስም መልሶ። የማታምን ጠማማ ትውልድ ሆይ፥ እስከ መቼ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ? እስከ መቼስ እታገሣችኋለሁ? ወደዚህ ወደ እኔ አምጡት አለ። ኢየሱስም ገሠጸው ጋኔኑም ከእርሱ ወጣ፥ ብላቴናውም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ተፈወሰ። ከዚህ በኋላ ደቀ መዛሙርቱ ብቻቸውን ወደ ኢየሱስ ቀረቡና። እኛ ልናወጣው ያልቻልን ስለ ምን ነው? አሉት። ኢየሱስም። ስለ እምነታችሁ ማነስ ነው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ተራራ። ከዚህ ወደዚያ እለፍ ብትሉት ያልፋል፤ የሚሳናችሁም ነገር የለም።”
ማቴ 17:14_20
“ እግዚአብሔርን ጽድቅ ሳያውቁ የራሳቸውንም ጽድቅ ሊያቆሙ ሲፈልጉ፥ ለእግዚአብሔር ጽድቅ አልተገዙም።የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና። ሙሴ ከሕግ የሆነውን ጽድቅ የሚያደርገው ሰው በእርሱ በሕይወት እንዲኖር ጽፎአልና። ከእምነት የሆነ ጽድቅ ግን እንዲህ ይላል። በልብህ። ማን ወደ ሰማይ ይወጣል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ለማውረድ ነው፤ ወይም። በልብህ። ወደ ጥልቁ ማን ይወርዳል? አትበል፤ ይህ ክርስቶስን ከሙታን ለማውጣት ነው።ነገር ግን ምን ይላል? በአፍህ በልብህም ሆኖ ቃሉ ቀርቦልሃል፤ ይህም የምንሰብከው የእምነት ቃል ነው።ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። መጽሐፍ። በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም ይላልና። በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ የጌታን ስም የሚጠራ ሁሉ ይድናልና። እንግዲህ ያላመኑበትን እንዴት አድርገው ይጠሩታል? ባልሰሙትስ እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ? መልካሙን የምሥራች የሚያወሩ እግሮቻቸው እንዴት ያማሩ ናቸው ተብሎ እንደ ተጻፈ ካልተላኩ እንዴት ይሰብካሉ? ነገር ግን ሁሉ ለምሥራቹ ቃል አልታዘዙም። ኢሳይያስ። ጌታ ሆይ፥ ምስክርነታችንን ማን አመነ? ብሎአልና። እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ዳሩ ግን። ባይሰሙ ነው ወይ? እላለሁ። በእውነት። ድምፃቸው በምድር ሁሉ ላይ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ። ነገር ግን። እስራኤል ባያውቁ ነው ወይ? እላለሁ። ሙሴ አስቀድሞ። እኔ ሕዝብ በማይሆነው አስቀናችኋለሁ በማያስተውልም ሕዝብ አስቆጣችኋለሁ ብሎአል። ኢሳይያስም ደፍሮ። ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፥ ላልጠየቁኝም ተገለጥሁ አለ። ስለ እስራኤል ግን። ቀኑን ሁሉ ወደማይታዘዝና ወደሚቃወም ሕዝብ እጆቼን ዘረጋሁ ይላል።
ሮሜ 10
“እንግዲህ ክፋትን ሁሉ ተንኰልንም ሁሉ ግብዝነትንም ቅንዓትንም ሐሜትንም ሁሉ አስወግዳችሁ፥ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ። በሰውም ወደ ተጣለ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ወደ ተመረጠና ክቡር ወደ ሆነው ወደ ሕያው ድንጋይ ወደ እርሱ እየቀረባችሁ፥እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ። በመጽሐፍ። እነሆ፥ የተመረጠና የከበረን የማዕዘን ራስ ድንጋይ በጽዮን አኖራለሁ በእርሱም የሚያምን አያፍርም ተብሎ ተጽፎአልና።እንግዲህ ክብሩ ለእናንተ ለምታምኑት ነው፤ ለማያምኑ ግን አናጢዎች የጣሉት ድንጋይ እርሱ የማዕዘን ራስ የዕንቅፋትም ድንጋይ የማሰናከያም ዓለት ሆነ፤ የማያምኑ ስለ ሆኑ በቃሉ ይሰናከሉበታልና፤ ለዚህ ደግሞ የተመደቡ ናቸው።እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል። ወዳጆች ሆይ፥ ነፍስን ከሚዋጋ ሥጋዊ ምኞት ትርቁ ዘንድ እንግዶችና መጻተኞች እንደ መሆናችሁ እለምናችኋለሁ፤ ስለሚመለከቱት ስለ መልካም ሥራችሁ፥ ክፉ እንደምታደርጉ በዚያ እናንተን በሚያሙበት ነገር፥ በሚጎበኝበት ቀን እግዚአብሔርን ያከብሩት ዘንድ በአሕዛብ መካከል ኑሮአችሁ መልካም ይሁን።ስለ ጌታ ብላችሁ ለሰው ሥርዓት ሁሉ ተገዙ፤ ለንጉሥም ቢሆን፥ ከሁሉ በላይ ነውና፤ለመኳንንትም ቢሆን፥ ክፉ የሚያደርጉትን ለመቅጣት በጎም የሚያደርጉትን ለማመስገን ከእርሱ ተልከዋልና ተገዙ። በጎ እያደረጋችሁ፥ የማያውቁትን ሞኞች ዝም ታሰኙ ዘንድ እንዲህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነውና፤አርነት ወጥታችሁ እንደ እግዚአብሔር ባሪያዎች ሁኑ እንጂ ያ አርነት ለክፋት መሸፈኛ እንዲሆን አታድርጉ።ሁሉን አክብሩ፥ ወንድሞችን ውደዱ፥ እግዚአብሔርን ፍሩ፥ ንጉሥን አክብሩ። ሎሌዎች ሆይ፥ ለበጎዎችና ለገሮች ጌቶቻችሁ ብቻ ሳይሆን ለጠማሞች ደግሞ በፍርሃት ሁሉ ተገዙ። በግፍ መከራን የሚቀበል ሰው እግዚአብሔርን እያሰበ ኃዘንን ቢታገሥ ምስጋና ይገባዋልና። ኃጢአት አድርጋችሁ ስትጎሰሙ ብትታገሡ፥ ምን ክብር አለበት? ነገር ግን መልካም አድርጋችሁ መከራን ስትቀበሉ ብትታገሡ፥ ይህ ነገር በእግዚአብሔር ዘንድ ምስጋና ይገባዋል። የተጠራችሁለት ለዚህ ነውና፤ ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሎአልና።እርሱም ኃጢአት አላደረገም፥ ተንኰልም በአፉ አልተገኘበትም፤ ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም መከራንም ሲቀበል አልዛተም፥ ነገር ግን በጽድቅ ለሚፈርደው ራሱን አሳልፎ ሰጠ፤ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤*ፍ1*በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል። ፍ1 በግዕዝ እንዲህ ተጽፎአል። ወበእንተ ኃጣውኢነ ውእቱ ተሰቅለ ዲበ ዕፅ በሥጋሁ ከመ ያውፅአነ እምኃጣውኢነ ወበጽድቁ ያሕይወነ።”
1 ጴጥ 2
1 ዮሐንስ ምዕራፍ 5
“ ክርስቶስ ነው ብሎ በኢየሱስ የሚያምን ሁሉ ከእግዚአብሔር ተወልዶአል፥ ወላጁንም የሚወድ ሁሉ ከእርሱ የተወለደውን ደግሞ ይወዳል።እግዚአብሔርን ስንወድ ትእዛዛቱንም ስናደርግ የእግዚአብሔርን ልጆች እንድንወድ በዚህ እናውቃለን።ትእዛዛቱን ልንጠብቅ የእግዚአብሔር ፍቅር ይህ ነውና፤ ትእዛዛቱም ከባዶች አይደሉም።ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ዓለምን ያሸንፋልና፤ ዓለምንም የሚያሸንፈው እምነታችን ነው። ኢየሱስም የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ከሚያምን በቀር ዓለምን የሚያሸንፍ ማን ነው? በውኃና በደም የመጣ ይህ ነው እርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ፤ በውኃውና በደሙ እንጂ በውኃው ብቻ አይደለም። መንፈስም እውነት ነውና የሚመሰክረው መንፈስ ነው።የሚመሰክሩት መንፈሱና ውኃው ደሙም ሦስት ናቸውና፤ ሦስቱም በአንድ ይስማማሉ።የሰውን ምስክር ብንቀበል የእግዚአብሔር ምስክር ከእርሱ ይልቅ ይበልጣል፤ ስለ ልጁ የመሰከረው የእግዚአብሔር ምስክር ይህ ነውና። በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምን በነፍሱ ምስክር አለው፤ በእግዚአብሔር የማያምን እግዚአብሔር ስለ ልጁ የመሰከረውን ምስክር ስላላመነ ሐሰተኛ አድርጎታል። እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው። ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም። የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ።በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል። የምንለምነውንም ሁሉ እንዲሰማልን ብናውቅ ከእርሱ የለመነውን ልመና እንደ ተቀበልን እናውቃለን።ማንም ወንድሙን ሞት የማይገባውን ኃጢአት ሲያደርግ ቢያየው ይለምን፥ ሞትም የማይገባውን ኃጢአት ላደረጉት ሕይወት ይሰጥለታል። ሞት የሚገባው ኃጢአት አለ፤ ስለዚያ እንዲጠይቅ አልልም። ዓመፃ ሁሉ ኃጢአት ነው፥ ሞትም የማይገባው ኃጢአት አለ።ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ ኃጢአትን እንዳያደርግ፥ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የተወለደው ራሱን እንዲጠብቅ ክፉውም እንዳይነካው እናውቃለን።ከእግዚአብሔር እንደ ሆንን ዓለምም በሞላው በክፉው እንደ ተያዘ እናውቃለን። የእግዚአብሔርም ልጅ እንደ መጣ፥ እውነተኛም የሆነውን እናውቅ ዘንድ ልቡናን እንደ ሰጠን እናውቃለን፤ እውነተኛም በሆነው በእርሱ አለን፥ እርሱም ልጁ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱ እውነተኛ አምላክና የዘላለም ሕይወት ነው። ልጆች ሆይ፥ ከጣዖታት ራሳችሁን ጠብቁ።
“ ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።ልጆች ሆይ፥ መጨረሻው ሰዓት ነው፥ የክርስቶስም ተቃዋሚ ይመጣ ዘንድ እንደ ሰማችሁ አሁን እንኳ ብዙዎች የክርስቶስ ተቃዋሚዎች ተነሥተዋል፤ ስለዚህም መጨረሻው ሰዓት እንደ ሆነ እናውቃለን።ከእኛ ዘንድ ወጡ፥ ዳሩ ግን ከእኛ ወገን አልነበሩም፤ ከእኛ ወገንስ ቢሆኑ ከእኛ ጋር ጸንተው በኖሩ ነበር፤ ነገር ግን ሁሉ ከእኛ ወገን እንዳልሆኑ ይገለጡ ዘንድ ወጡ።እናንተም ከቅዱሱ ቅባት ተቀብላችኋል፥ ሁሉንም ታውቃላችሁ።እውነትን የምታውቁ ስለ ሆናችሁ፥ ውሸትም ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን ስለማታውቁ አልጽፍላችሁም። ክርስቶስ አይደለም ብሎ ኢየሱስን ከሚክድ በቀር ውሸተኛው ማን ነው? አብንና ወልድን የሚክድ ይህ የክርስቶስ ተቃዋሚ ነው።ወልድን የሚክድ ሁሉ አብ እንኳ የለውም፤ በወልድ የሚታመን አብ ደግሞ አለው።እናንተስ ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ጸንቶ ይኑር። ከመጀመሪያ የሰማችሁት በእናንተ ቢኖር፥ እናንተ ደግሞ በወልድና በአብ ትኖራላችሁ። እርሱም የሰጠን ተስፋ ይህ የዘላለም ሕይወት ነው።ስለሚያስቱአችሁ ሰዎች ይህን ጽፌላችኋለሁ። እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፥ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፥ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፥ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፥ በእርሱ ኑሩ። አሁንም፥ ልጆች ሆይ፥ በሚገለጥበት ጊዜ እምነት እንዲሆንልን በመምጣቱም በእርሱ ፊት እንዳናፍር በእርሱ ኑሩ። ጻድቅ እንደ ሆነ ካወቃችሁ ጽድቅን የሚያደርግ ሁሉ ከእርሱ እንደ ተወለደ እወቁ።”
1 ዮሐ 2:15_29
“ የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፥ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ ክርስቶስ እንደ ተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ አዚም ያደረገባችሁ ማን ነው? ይህን ብቻ ከእናንተ እንድማር እወዳለሁ፤ በሕግ ሥራ ወይም ከእምነት ጋር በሆነ መስማት መንፈስን ተቀበላችሁን? እንዲህን የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን? በውኑ ከንቱ እንደ ሆነስ እንደዚህ ያለ መከራ በከንቱ ተቀበላችሁን? እንግዲህ መንፈስን የሚሰጣችሁ በእናንተም ዘንድ ተአምራት የሚያደርግ፥ በሕግ ሥራ ነውን ወይስ ከእምነት ጋር በሆነ መስማት ነው? እንዲሁ አብርሃም በእግዚአብሔር አመነና ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። እንኪያስ ከእምነት የሆኑት እነዚህ የአብርሃም ልጆች እንደ ሆኑ እወቁ። መጽሐፍም እግዚአብሔር አሕዛብን በእምነት እንዲያጸድቅ አስቀድሞ አይቶ። በአንተ አሕዛብ ሁሉ ይባረካሉ ብሎ ወንጌልን ለአብርሃም አስቀድሞ ሰበከ። እንደዚህ ከእምነት የሆኑት ካመነው ከአብርሃም ጋር ይባረካሉ። ከሕግ ሥራ የሆኑት ሁሉ በእርግማን በታች ናቸውና፤ በሕግ መጽሐፍ በተጻፉት ሁሉ ጸንቶ የማይኖር የማያደርግም ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና። ጻድቅ በእምነት ይኖራል ተብሎአልና ማንም በእግዚአብሔር ፊት በሕግ እንዳይጸድቅ ግልጥ ነው። ሕግም ከእምነት አይደለም ነገር ግን። የሚያደርገው ይኖርበታል ተብሎአል።በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤ የመንፈስን ተስፋ በእምነት እንድንቀበል፥ የአብርሃም በረከት ወደ አሕዛብ በኢየሱስ ክርስቶስ ይደርስላቸው ዘንድ። ወንድሞች ሆይ፥ እንደ ሰው ልማድ እላለሁ። የሰው ስንኳ ቢሆን እርግጠኛውን ኪዳን ማንም አይንቅም ወይም አይጨምርበትም። ለአብርሃምና ለዘሩም የተስፋው ቃል ተነገረ። ስለ ብዙዎች እንደሚነገር። ለዘሮቹም አይልም፤ ስለ አንድ እንደሚነገር ግን። ለዘርህም ይላል፥ እርሱም ክርስቶስ።ይህንም እላለሁ፤ ከአራት መቶ ሠላሳ ዓመት በኋላ የተሰጠው ሕግ አስቀድሞ በእግዚአብሔር የተረጋገጠውን ኪዳን የተስፋውን ቃል እስኪሽር ድረስ አያፈርስም። ርስቱ በሕግ ቢሆንስ እንግዲያስ በተስፋ ቃል አይሆንም፤ በተስፋ ቃል ግን እግዚአብሔር ለአብርሃም ሰጥቶአል። እንግዲህ ሕግ ምንድር ነው? ተስፋው የተሰጠው ዘር እስኪመጣ ድረስ በመካከለኛ እጅ በመላእክት በኩል ስለ ሕግ መተላለፍ ተጨመረ። መካከለኛውም ለአንድ ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ግን አንድ ነው። እንግዲህ ሕግ የእግዚአብሔርን የተስፋ ቃል የሚቃወም ነውን? አይደለም። ሕያው ሊያደርግ የሚቻለው ሕግ ተሰጥቶ ቢሆንስ በእውነት ጽድቅ ከሕግ በሆነ ነበር፤ ነገር ግን በኢየሱስ ክርስቶስ ከማመን የሆነው የተስፋ ቃል ለሚያምኑ ይሰጥ ዘንድ መጽሐፍ ከኃጢአት በታች ሁሉን ዘግቶታል። እምነትም ሳይመጣ ሊገለጥ ላለው እምነት ተዘግተን ከሕግ በታች እንጠበቅ ነበር። እንደዚህ በእምነት እንጸድቅ ዘንድ ሕግ ወደ ክርስቶስ የሚያመጣ ሞግዚታችን ሆኖአል፤እምነት ግን መጥቶአልና ከእንግዲህ ወዲህ ከሞግዚት በታች አይደለንም። በእምነት በኩል ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጆች ናችሁና፤ከክርስቶስ ጋር አንድ ትሆኑ ዘንድ የተጠመቃችሁ ሁሉ ክርስቶስን ለብሳችኋልና። አይሁዳዊ ወይም የግሪክ ሰው የለም፥ ባሪያ ወይም ጨዋ ሰው የለም፥ ወንድም ሴትም የለም፤ ሁላችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ አንድ ሰው ናችሁና።እናንተም የክርስቶስ ከሆናችሁ እንኪያስ የአብርሃም ዘር እንደ ተስፋውም ቃል ወራሾች ናችሁ።”
ገላ 3
“ ዳዊትም። ከአንበሳና ከድብ እጅ ያስጣለኝ እግዚአብሔር ከዚህ ፍልስጥኤማዊ እጅ ያስጥለኛል አለ። ሳኦልም ዳዊትን። ሂድ፥ እግዚአብሔርም ከአንተ ጋር ይሆናል አለው።”
1 ሳሙ 17:37
“ እንግዲህ፥ ወንድሞች ሆይ፥ በመረቀልን በአዲስና በሕያው መንገድ ወደ ቅድስት በኢየሱስ ደም በመጋረጃው ማለት በሥጋው በኩል እንድንገባ ድፍረት ስላለን፥ በእግዚአብሔርም ቤት ላይ የሆነ ታላቅ ካህን ስላለን፥ ከክፉ ሕሊና ለመንጻት ልባችንን ተረጭተን ሰውነታችንንም በጥሩ ውኃ ታጥበን በተረዳንበት እምነት በቅን ልብ እንቅረብ:: ”
ዕብ 10:19_22
“ እብዶች ብንሆን፥ ለእግዚአብሔር ነው፤ ባለ አእምሮዎች ብንሆን፥ ለእናንተ ነው።ይህን ስለቆረጥን የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናልና፤ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ እንግዲያስ ሁሉ ሞቱ፤በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ።ስለዚህ እኛ ከአሁን ጀምሮ ማንንም በሥጋ እንደሚሆን አናውቅም፤ ክርስቶስንም በሥጋ እንደ ሆነ ያወቅነው ብንሆን እንኳ፥ አሁን ግን ከእንግዲህ ወዲህ እንደዚህ አናውቀውም። ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን አይቆጥርባቸውም ነበር፤ በእኛም የማስታረቅ ቃል አኖረ። እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን።እኛ በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።”
1 ቆሮ 5:13_21
የዲያብሎስ ሀይማኖታዊ የእምነት ፈውስ
“ አምላክህ እግዚአብሔር ወደሚሰጥህ ምድር በገባህ ጊዜ እነዚያ አሕዛብ የሚያደርጉትን ርኵሰት ታደርግ ዘንድ አትማር። ወንድ ልጁን ሴት ልጁን በእሳት የሚያሳልፍ፥ ምዋርተኛም፥ ሞራ ገላጭም፥አስማተኛም፥ መተተኛም፥ በድግምት የሚጠነቍልም፥ መናፍስትንም የሚጠራ፥ ጠንቋይም፥ ሙታን ሳቢም በአንተ ዘንድ አይገኝ። ይህንም የሚያደርግ ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት የተጠላ ነው፤ ስለዚህም ርኵሰት አምላክህ እግዚአብሔር ከፊትህ ያሳድዳቸዋል። አንተ ግን በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ ፍጹም ሁን::”
ዘዳ 18:9_13
1ዮሐንስ ምዕራፍ 4
ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና። የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ። ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና። እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል። እኛ ከእግዚአብሔር ነን፤ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል፤ ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም። የእውነትን መንፈስና የስሕተትን መንፈስ በዚህ እናውቃለን። ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ። ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና። ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም። ወዳጆች ሆይ፥ እግዚአብሔር እንዲህ አድርጎ ከወደደን እኛ ደግሞ እርስ በርሳችን ልንዋደድ ይገባናል።እግዚአብሔርን ማንም ከቶ አላየውም፤ እርስ በርሳችን ብንዋደድ እግዚአብሔር በእኛ ይኖራል ፍቅሩም በእኛ ፍጹም ሆኖአል። ከመንፈሱ ስለ ሰጠን፥ በእርሱ እንድንኖር እርሱም በእኛ እንዲኖር በዚህ እናውቃለን። እኛም አይተናል አባትም ልጁን የዓለም መድኃኒት ሊሆን እንደ ላከው እንመሰክራለን። ኢየሱስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ በሚታመን ሁሉ እግዚአብሔር በእርሱ ይኖራል እርሱም በእግዚአብሔር ይኖራል። እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል።በፍርድ ቀን ድፍረት ይሆንልን ዘንድ ፍቅር በዚህ ከእኛ ጋር ተፈጽሞአል፤ እርሱ እንዳለ እኛ ደግሞ እንዲሁ በዚህ ዓለም ነንና። ፍጹም ፍቅር ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላል እንጂ በፍቅር ፍርሃት የለም፥ ፍርሃት ቅጣት አለውና፤ የሚፈራም ሰው ፍቅሩ ፍጹም አይደለም። እርሱ አስቀድሞ ወዶናልና እኛ እንወደዋለን። ማንም። እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል? እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ ይህች ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።
2 ጴጥ ምዕራፍ 2
ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል።ገንዘብንም በመመኘት በተፈጠረ ነገር ይረቡባችኋል፤ ፍርዳቸውም ከጥንት ጀምሮ አይዘገይም ጥፋታቸውም አያንቀላፋም።እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሃነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው፥ለቀደመውም ዓለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን አድኖ በኃጢአተኞች ዓለም ላይ የጥፋትን ውኃ ካወረደ፥ኃጢአትንም ያደርጉ ዘንድ ላሉት ምሳሌ አድርጎ ከተማዎችን ሰዶምንና ገሞራን አመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጥሎና ገልብጦ ከፈረደባቸው፥ጻድቅ ሎጥም በመካከላቸው ሲኖር እያየና እየሰማ ዕለት ዕለት በዓመፀኛ ሥራቸው ጻድቅ ነፍሱን አስጨንቆ ነበርና በዓመፀኞች ሴሰኛ ኑሮ የተገፋውን ያን ጻድቅ ካዳነ፥ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል። ደፋሮችና ኵሩዎች ሆነው ሥልጣን ያላቸውን ሲሳደቡ አይንቀጠቀጡም፤ዳሩ ግን መላእክት በኃይልና በብርታት ከእነርሱ ይልቅ ምንም ቢበልጡ በጌታ ፊት በእነርሱ ላይ የስድብን ፍርድ አያመጡም።እነዚህ ግን ለመጠመድና ለመጥፋት በፍጥረታቸው እንደ ተወለዱ አእምሮ እንደ ሌላቸው እንስሶች ሆነው፥ በማያውቁት ነገር እየተሳደቡ በጥፋታቸው ይጠፋሉ፤የዓመፃቸውን ደመወዝ ይቀበላሉ። በቀን ሲዘፍኑ እንደ ተድላ ይቆጥሩታል፤ ነውረኞችና ርኵሳን ሆነው ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣ ይዘፍናሉ፤ምንዝር የሞላባቸው ኃጢአትንም የማይተዉ ዓይኖች አሉአቸው፤ የማይጸኑትን ነፍሳት ያታልላሉ፤ መመኘትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ናቸው።ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ፤ የባሶርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከተሉ፤ እርሱ የዓመፃን ደመወዝ ወደደ፥ነገር ግን ስለ መተላለፉ ተዘለፈ፤ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነቢዩን እብድነት አገደ።ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው እነዚህ ውኃ የሌለባቸው ምንጮች በዐውሎ ነፋስም የተነዱ ደመናዎች ናቸው።ከንቱና ከመጠን ይልቅ ታላቅ የሆነውን ቃል ይናገራሉና፥ በስሕተትም ከሚኖሩት አሁን የሚያመልጡትን በሥጋ ሴሰኛ ምኞት ያታልላሉ።ራሳቸው የጥፋት ባሪያዎች ሆነው። አርነት ትወጣላችሁ እያሉ ተስፋ ይሰጡአቸዋል፤ ሰው ለተሸነፈበት ለእርሱ ተገዝቶ ባሪያ ነውና።በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና።ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ። የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል።
1ጢሞ ምዕራፍ 4
መንፈስ ግን በግልጥ። በኋለኞች ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንትን ትምህርት እያደመጡ፥ ሃይማኖትን ይክዳሉ ይላል፤ በገዛ ሕሊናቸው እንደሚቃጠሉ ደንዝዘው፥እነዚህ ውሸተኞች መጋባትን ይከለክላሉ፥ አምነውም እውነትን የሚያውቁ ከምስጋና ጋር ይቀበሉ ዘንድ እግዚአብሔር ከፈጠረው መብል እንዲርቁ ያዝዛሉ።እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም ነውና፥ ከምስጋናም ጋር ቢቀበሉት የሚጣል ምንም የለም፤በእግዚአብሔር ቃልና በጸሎት የተቀደሰ ነውና። ስለዚህ ወንድሞችን ብታሳስብ፥ በእምነትና በተከተልኸው በመልካም ትምህርት ቃል የምትመገብ የኢየሱስ ክርስቶስ መልካም አገልጋይ ትሆናለህ።ነገር ግን ለዚህ ዓለም ከሚመችና የአሮጊቶችን ሴቶች ጨዋታ ከሚመስለው ተረት ራቅ። እግዚአብሔርን ለመምሰል ግን ራስህን አስለምድ።ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው፥ ለነገር ሁሉ ይጠቅማል።ይህ ቃል የታመነ ሁሉም እንዲቀበሉት የተገባ ነው፤ይህን ለማግኘት እንደክማለንና፥ ስለዚህም እንሰደባለን፤ ይህም ሰውን ሁሉ ይልቁንም የሚያምኑትን በሚያድን በሕያው አምላክ ተስፋ ስለምናደርግ ነው። ይህን እዘዝና አስተምር። በቃልና በኑሮ በፍቅርም በእምነትም በንጽሕናም ለሚያምኑቱ ምሳሌ ሁን እንጂ፥ ማንም ታናሽነትህን አይናቀው። እስክመጣ ድረስ ለማንበብና ለመምከር ለማስተማርም ተጠንቀቅ።በትንቢት ከሽማግሌዎች እጅ መጫን ጋር የተሰጠህን፥ በአንተ ያለውን የጸጋ ስጦታ ቸል አትበል።ማደግህ በነገር ሁሉ እንዲገለጥ ይህን አስብ፥ ይህንም አዘውትር።ለራስህና ለትምህርትህ ተጠንቀቅ፥ በእነዚህም ጽና፤ ይህን ብታደርግ፥ ራስህንም የሚሰሙህንም ታድናለህና።
ይህን ሁለቱን ፈውሶች ከመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ካየነው ዘንዳ ወደ መንፈሳዊው የኦርቶዶክስ እምነት ፈውስ ሰጭ መምህር ግርማ የፈውስ ስራ ስመጣ ፈውስ በሚመስልም ሌሎችን ለመስበክና ለማሳሳት የዲያብሎስ ፈውስ ማሳሳቻ እንደሆነ ሁላችን እንድንረዳ ያስፈልጋል:: ምክንያቱም መምህር ግርማ ጋር ብዙ ግዜ ሀይማኖታዊ ንግግር ሲያደርጉ የምናያቸው የአጋንንት መንፈሶች ሁሉንም በደንብ አድርገን ካስተዋልን እርኩሳን መናፍስቶቹ ሁሉ የሚለቀቁት ከሟርተኞችና ከደጋሚዎች ነው:: ሁል ጊዜ ለማለት ይቻላል ከላይ ስለ ኦርቶዶክስ እና ኢስላም ሀይማኖት ከድግምትና ከመተት ጋር ያላቸውን ትስስር ለመነሻ እንደተናገርኩት መምህር ግርማ ጋር ለሽምግልና የሚመጡት ሰዎች ሁሉ በየጦንቃዩና በየደጋሚው ቤት የገቡትን ቃለ መሀላ ሲያፈርሱ ያ እርኩስ መንፈስ ቃልኪዳን ያፈረሱትንና አሳስሮ ሽባ ያደረጋቸውን እነዚያን በሽተኞች የቀድሞውን የድግምት ውላቸውን ለማደስ በመምህር ግርማ በኩል በሀይማኖታዊ ፈውስ አማካኝነት የእርቅ አገልግሎት እንዲያገኙ ይደረጋሉ:: ለዚህ ደግሞ በእዚህ መንፈስ ተጠቂ የሆነችዋንና ከእዚህ እርኩስ የድግምት መንፈስ እግዚያብሔር ነጻ ያወጣትን ተአምር የሆነ የመተት ህይወት የናበራትን መስካሪያችንን በሱማሌ ክልል ነዋሪና በታዋቂ ጦንቃይ መተት በአንድ ወቅት አስመጪና ላኪ የሆነችዋና ከአክራሪው የሙስሊም ቤተሰብ የተወለደችው ሮውዳ ድንቅ ምስክሯን እንዲህ በማለት ታሰማናለች::

የእዚህ ጽሁፍ ዋና አላማ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ትክክለኛውንና እውነተኛውን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የተገለጸውን የእግዚያብሔርን ቃልና የፈውስ ደህንነት እንዲያገኙ ለማመላከት ነው:: ስለሆነም መምህር ግርማን ጨምሮ ያልዳኑት የኦርቶዶክስ እና የሙስሊም ወንድሞቻችን ወደእውነተኛው የእግዚያብሔር ቃል በመምጣት እንዲሁ የአጋንንትን ከንቱ የማስታረቅ ንግግር አይተው በከንቱ ዘመኖቻቸው እንዳያልቅና ወደ ፍርድ እንዳይቀርቡ እንዲሁ ደግሞ በክርስቶስ ኢየሱስ ለሁሉም ከተሰጠው ከዘላለም ህይወት እንዳይጓደሉ ትክክለኛው የእምነት ቃል ሐይማኖትም ግዴታ ስላለብንም ጭምር ነው ይህንን የእውነት ትክክለኛውን ወንጌል የምንሰብከው:: ነገርግን ፈርተናቸው ብዙ ቤተሰቦቻችን : ዘመዶቻችንና ጓደኞቻችንን አስፈረድንባቸው ዛሬ ግን ማንኛውንም የሚመጣውን ነገር ለመቀበል የወንጌልን የእውነትቃል በድፍረት እንናገራለን ወንጌል ያድናል እንላለን እንሰብካለን : እንመሰክራለን በስተመጨረሻም ስለእውነተኛው ወንጌል የሚደርስብንን ጊዚያዊ ፈተና በደስታ እንቀበላለን ስለሆነም የተቀበልነው የእውነት መንፈስ ነውና እንዴት ዝም እንድንል እንችላለን? ስለዚህ ሁሌም በጌታ ያልሆናችሁት ወንድሞቻችንና እህቶቻችን በጌታ ፍቅር እኛ የእግዚያብሔር ልጆች እንወዳችኋለን እንጸልይላችኋለን::
“በመንፈስ ተመላለሱ፥ የሥጋንም ምኞት ከቶ አትፈጽሙ።ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስም በሥጋ ላይ ይመኛልና፥ እነዚህም እርስ በርሳቸው ይቀዋወማሉ፤ ስለዚህም የምትወዱትን ልታደርጉ አትችሉም።በመንፈስ ብትመሩ ግን ከሕግ በታች አይደላችሁም። የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵሰት፥ መዳራት፥ ጣዖትን ማምለክ፥ ምዋርት፥ ጥል፥ ክርክር፥ ቅንዓት፥ ቁጣ፥ አድመኛነት፥ መለያየት፥ መናፍቅነት፥ ምቀኝነት፥ መግደል፥ ስካር፥ ዘፋኝነት፥ ይህንም የሚመስል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፥ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።የክርስቶስ ኢየሱስም የሆኑቱ ሥጋን ከክፉ መሻቱና ከምኞቱ ጋር ሰቀሉ።በመንፈስ ብንኖር በመንፈስ ደግሞ እንመላለስ።እርስ በርሳችን እየተነሣሣንና እየተቀናናን በከንቱ አንመካ።” ገላ 5:16_26
“ ንግግሬን የማታስተውሉ ስለ ምንድር ነው? ቃሌን ልትሰሙ ስለማትችሉ ነው።እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና።እኔ ግን እውነትን የምናገር ስለ ሆንሁ አታምኑኝም።”
ዮሐ 8:43_45
በመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ያለ ፈውስና ተአምራት በሙሉ የፈውስና የተአምራት ምንጩ ዲያብሎስ ነው::!

የክርስትያኖች ጠላት እራሳችን ክርስትያኖች ነን! “ እነሆ ከአዳም ጎድን አንድ አጥንት ወጥታ እስከ አሁን ድረስ ትጠዘጥዘናለች ”

400e8ad81bfc57bc7e4c12a9ec6af50f

“ ነቢያት በሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፥ ካህናትም በእነዚህ እጅ ይገዛሉ፥ ሕዝቤም እንዲህ ያለውን ነገር ይወድዳሉ፤ በፍጻሜውስ ምን ታደርጋላችሁ?” ኤር 5:31
ከላይ እንደመግቢያ የተጠቀምኩበት በነብዬ ኤርሚያስ ስለ ሀሰተኞች ነቢያትና አስተማሪዎች የተነገረው የእግዚያብሔር የትንቢት ቃል እነሆ ስሩን ሰዶ ዛሬ ላይ በየአብያተ ቤተክርስትያኑ ጥሩ የንግድ ማስታወቂያ ትርፍ ከሆነ ሰነባበተ::
imagesLS95RMWS
በመጽሐፍ ቅዱሳችን ላይ ስለ እግዚያብሔር ነቢያቶችና አስተማሪዎች እንዲሁም ስለ ሀሰተኞቹ ነቢያቶችና አስተማሪዎች በግልጽ ተጽፎዋል:: ብዙ ግዜ እኛ በክርስቶስ ኢየሱስ የዳግም ውልደት ክርስትናን የተቀበልን ክርስትያኖች የሚመስለን ዳግም ያልተወለደውን የየትኛውንም ሀይማኖት ተከታይ በሙሉ ሀሰተኛ አስተማሪና ነብይ አድርገን እናያለን በእርግጥ እውነት ነው:: እነዚያ ትክክለኛውን የወንጌልን ቃል የማያስተምሩና ዳግም ውልደትን ያላገኙ በሙሉ የሀሰተኛ ትምህርት አስተማሪዎችና ከዚያም አልፎ ከራሳቸው ስጋዊ ሀሳበ መለኮት በመነሳትና እግዚያብሔር የተናገረ በማስመሰል የውሸት ትንቢት የሚናገሩም ነቢያቶችም ጭምር ናቸው::
እግዚያብሔር ብዙ ግዜ ስለሀሰተኛ ትንቢተኞችና ወንጌል ሰባኪዎች የሚነግረንና እንድንጠነቀቅ የሚያሳስበን በቤቱ ካለን ወይም በክርስቶስ ኢየሱስ የዳግም ውልደትን ያገኘን አሊያም በግልጽ አማርኛ እኛ ጴንጤዎችን ነው:: በእዚህ ባለንበት የመጨረሻ የፍርድ ሰአት ነገሮች ሁሉ መልካቸውን ቀይረው እንደተባለው በመጨረሻው ዘመን በምድር ላይ ከሚገለጹ ምልክቶች አንዱና ዋናው የሀሰተኛ ነቢያቶችና አስተማሪዎች መነሳትና እንደ አሸን መፍላት ነው:: ስለዚህም ትንቢት ጌታ ኢየሱስ በግልጽ ቋንቋ የትንቢት ቃሉን እንዲህ በማለት ሰጥቶናል::
“ በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል።መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት፥ ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም።መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ።በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። የዚያን ጊዜም። ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።” ማቴ 7:13_23
RIAPD%20Masthead
እነዚህ ጌታ ኢየሱስ የተናገራቸው ትንቢተኞች በስሙ ብዙ ተአምራት እንዳደረጉና እርሱ ግን ሲክዳቸው እናያለን:: ለምን እንደካዳቸው ከላይ የተገለጸ ሲሆን ለዚህ ስለጌታ ኢየሱስ ቃል በጌታ የተመረጠውና የተወደደው እግዚያብሔር ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስም በመልእክቱ እንዲህ በማለት ይገልጸዋል::
“ ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል።እኛ ከእግዚአብሔር ነን፤ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል፤ ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም። የእውነትን መንፈስና የስሕተትን መንፈስ በዚህ እናውቃለን።” 1 ዮሐ 4:1—6
10352337_892793134068577_520376606312612661_n
እዚህ ላይ የሐዋርያው የጳውሎስ መልእክት በግልጽ እንደሚናገረው ስለአለምና ስለስጋ ነገር ትንቢት የሚናገርና የሚያስተምር እርሱ ሀሰተኛ ነቢይና ሀሰተኛ የወንጌል አስተማሪ ነው:: ሁላችንም እንደምናውቀው የቅርብ ግዜ በመዲናችን አዲስ አበባ የዲያብሎስ ነቢይ ቡሽሪ (ቡሽራ) ተፈጸመ የተባለው በጣም ጸያፍ የተባለ እምነታዊ ሳይሆን ሀይማኖታዊ ስጋዊ ክርስቲያናዊ ውንብድና ስራ የብዙዎቻችንን አንገት አስደፍቷል:: አህዛቦች ሁሉ ተሳልቀውብናል ለስጋዊ መስገብገብና ለከርሳችን የአምላካችንን የእግዚያብሔርን ስም አስድበናል ንጹህ ህሊና ቢኖረን ኖሮ ለዚህ ጸያፍ ስራችን ልብሳችንን ቀደን ማቅ ለብሰን አመድ ነስንሰን ወደ እግዚያብሔር በጮህን ነበር:: ነገር ግን ዛሬም የያዘን ክፉ መንፈስ አለቅ ብሎን ኧረ! የነቢይ ያለህ እንላለን ይህንን ነቢይ የምንፈልገው ወደ እግዚያብሔር መንገድ ገስጾ እንዲመራን ሳይሆን ወደ አለም እንዲመራንና የአለም ነገሮች ሁሉ ወደ ህይወታችን እንዲያመጣልን ነቢይ እከሌ የተባለ ማስታወቂያ ሁሉ በተነገረበት በር ሁሉ ሁሌም ከስጋ ቤት በራፍ የማትጠፋና የምትቁለጨለጭ ውሻ ከሆንን ሰነባብተናል:: በተለይ በተለይ ሴቶች እህቶቻችን !
ከዘፍጥረት ከወደቀችው ሄዋን ጀምሮ እስከ በራእይ በክፋቷና በጸያፍ ስራዋ እስከምትገለጠው ጋለሞታይቱ ሴት ድረስ ሴቶች ትልቅ የሰይጣን መልእክተኞች በመሆን ዲያብሎስን ያገለግሉታል በተለይ በእግዚያብሔር ቤት ያሉ ሴት እህቶቻችን ይጠቀሳሉ::
erica-campbell-dress
በእግዚያብሔር ቤት ያሉ ሴት እህቶቻችን እስከ አሁኗ ሰአት ደረስ ራሳቸውን አሳልፈው ለታላቁ ጌታ አልሰጡም በአጭር አማርኛ አልዳኑም ወይም እራሳቸውን እናታቸው ሄዋን የሰራችውን ሀጢያት አልካዱም ይህንን የምጽፈው በድፍረት ነው:: ማንኛውም የዳነ ክርስቲያን ስለመዳኑ ማረጋገጫው በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈውን የእግዚያብሔርን ቃል ትእዛዝ በመረዳት በህይወቱ የተገለጠ ሁሉም የሚያየው ክርስትናዊ ህይወት ይኖራል:: ከእነዚህም መካከል ተለይተው የጌታ ደህንነት ያገኙ ሴት እህቶቻችን ማድረግ ያለባቸውንና የሌለባቸውን በግልጽ እግዚያብሔር ተናግሯል:: ከእነዚህ አንዱና ዋነው ክርስቲያን ሴቶች በየትኛውም ቦታ ስለሚለብሱት ልብስና ስለሚጋጋጡበት ጌጣ ጌጥ ነው::
በየጉባኤው የምናየው የእህቶቻችን የአለባበስ ስርአት መረን ከለቀቀና ቅጥ አንባሩ ከጠፋ ሰነባበተ ወደ በጭፈራ ቤት የሚሄዱ አለማውያን ሴት እህቶቻችን እስኪቀኑባቸው ድረስ ፓ! መልበስስ እንደ ጴንጤ ሴት ከተባለ ሰነበተ ምን መልበስ ብቻ መብላት : መጠጣት : መጨፈር : መዘሞትና አለማዊነት እንደ ጴንጤ ሴቶች ከተባለና አለማውያኖች እንኳ በእኛ ሀጢያት ሲቀኑ ማየት አሁን አሁን የተለመደ ባህላዊ ክስተት ከሆነ ሰናባብቷል:: እዚህ ላይ ሴቶች እህቶቻችንን አስቀደምኩ እንጂ እኛም ወንዶቹ ከእናንተ በሚያስቀና መልኩ በብልታችን ማምለክ ከጀመርን ሰነባበትን እዚህ ላይ ሰፊውን የሀጢያት ማሳሳቻ የስራ ድርሻ የሚወስዱት ሴቶች እህቶቻችን ናቸው:: ምክንያቱም የእግዚያብሔር ቃል እንደሚለን
men-staring-at-woman
“ ዓይንህ ብታሰናክልህ አውጣት፤ ሁለት ዓይን ኖሮህ ትላቸው ወደማይሞትበት እሳቱም ወደማይጠፋበት ወደ ገሃነመ እሳት ከመጣል አንዲት ዓይን ኖራህ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት ይሻልሃል።” ይህ ማለት ምንድ እህቶቻችን ደረታቸው ከፍተው ጡታቸውን እያሳዬ እንዲሁም ጭናቸውን የሚያሳይ አጭር ቀሚስና ሙሉ ተክለ ስጋቸውን በደንብ አውጥቶ የሚያሳይና በተጨማሪ በልዬ ልዬ አለማዊ ማጋጌጫዎች ተጋጊጠውና ውበት የሆናቸውን ጸጉራቸውን ነስንሰው ወደ ጉባኤ ሲገቡ ያያቸው ሁሉ በስጋ አምሮት ክፉኛ ይሰቃያል ደግሞም ከአገልጋዩ ፊት ከሆነ ቦታቸው (ብዙ ግዜ ከፊት ነው የሚሆኑት) አገልጋዩ በሄዋን የሰይጣን ፈተና መከራውን ይበላል ስንቶቹ የእግዚያብሔር አገልጋዮች በዚህ ክፉ ፍላጻ ተወግተው ከመንፈሳዊ ህይወት እንደጠፉ ጉባኤው ይቁጠረው::
michelangelo_original_sin_l
ይህንን ሁሉ ያመጡት የእግዚያብሔር ቤት አገልጋይ ነን ባዮች በድፍረትና ለቃሉ ባለመታዘዝ ያመጡት መቅሰፍት ነው::
83_100707_ds_ministermoneytn.jpg.CROP.original-original
ዛሬ እነዚህ የእግዚያብሔር ቤት አገልጋዮች ነን ባዮች ሀሰተኛ ነቢያቶችና አስተማሪዎች ስለአገልግሎታቸው የጥራት ድጋፍና ሙገሳ ክርስቲያናዊ ጥቅማ ጥቅም ሁሌም የሚጠብቁት : የሚያገኙት በብዛት ከክርስትያን እህቶቻችን ነው ባጭሩ ለአሁን ዘመን በየቤተክርስቲያኑ ራሳቸውን ነቢይና መጋቢ አድርገው ለቀቡ አፍአዊና ስጋዊ ክርስቲያኖች ደረጃ መዳቢዮቻቸውና ቁጥር አንድ ደጋፊዎቻቸው ክርስቲያን እህቶቻችን ናቸው ስለዚህ “ውሻ በበላበት ይጮኃል” እንደሚባለው ብዙ ግዜ ክርስቲያን ሴት እህቶቻችን የሚያመልኩት ሰዎችን ነው ሰዎችን ስላችሁ በመጀመሪያ እራሳቸውን ቀጥለው የሚወዱትን ሰባኪያቸውን አሊያም ነቢያቸውን የሚወዱትን ዘማሪ በተለይ አገልጋዮቹ ጮሌዎችና ቄንጠኛ ከሆኑ በተጨማሪም አገልጋዮቹ እንደነ ክበበው ገዳ : ፍልፍሉና መስከረም በቀለ ያሉ ኮሜዲያን ፓስተሮች በክርስቲያን እህቶቻችን ዘንድ እጅግ እጅግ ተመረጭ ናቸው:: ለዚህም አገልጋዮቻችን ከመጽሀፍ ቅዱስ ጥናት ውጭ ቀልድ : ፌዝና አስቂኝ የቃላት አረፍተ ነገሮችን ማጥናት ይጠበቅባቸዋል::
ysakalchuwal edited
ብዙ ግዜ ክርስትያን በእህቶቻችን የሚመረጡ አገልጋዮችን ለማግኘት በክርስቲያን ሴቶች በኩል ማለፍ ግድ ይላል:: ብዙ ግዜ በክርስቲያን እህቶቻችን የሚወደዱ አገልጋዮች አገልግሎታቸው ከሆስተሶች ተለይቶ አይያይም በተጨማሪም ለዚህም በእህቶቻችን ክፉ መንፈሳዊ አባዜ ለማስፈጸም በዲያብሎስ መሰሪ እቅድና ሀሳብ መሰረት በየመነደሩና በየጉራንጉሩ የመጨረሻው ሰአት ሀሰተኛ ነቢያቶችና አስተማሪዎች በክርስቲያን እህቶቻችን ብርቱ ፍላጎት ምክንያት እንደጉድ ተፈልፍለዋል::

ሌላው ብዙ ግዜ የክርስቲያን እህቶቻችን ተመረጭ አገልጋዮች የፌስ ቡክ ፕሮፋይል ፎቶዎች ያሸበረቁ ሲሆን ብዙዎቹ ከአምልኮ በማይለይ መልኩ ያሞካሹዋቸዋል : ያንቆለጳጵሱዋቸዋል ከዚያም ባለፈ ስጋዊ በሚመስል ፍላጎት ስማቸውን ጠርተው ያቆላምጡዋቸዋል ዛሬ ዛሬ በተለይ በውጭ አገር ያሉ ክርስቲያን እህቶቻችን ክርስቲያን ወንድሞችን በተለይ አገልጋዮችን ባለትዳር እንደሆኑ እያወቁ እንኳ እንደ ሰፈር የመንደር ጎረምሳ መውጫ መግቢያ ያሳጧቸዋል::
ሌላው ክርስትያን እህቶቻችን ብቻ ሳይሆኑ አብዛዎቻችን የሚገስጹንን : የሚያንጹንን ወደ ትክክለኛው የእግዚያብሔር መንገድ የሚመሩንን ሰባኪዎችንና ትምህርቶችን አንወድም በተቃራኒው ደግሞ ስለ ስጋና ስለ አለም ነገር እንድንፈልግ የሚያስተምሩንን ሰባኪዎችና ስብከቶች እንወዳቸዋለን ሌላው ቢቀር የቪዲዮ ስብከታቸውን እንኳ ደጋግመን እናየዋለን እዚህ ላይ ለምሳሌ ለማሳየት የፈለግኩት በአንድ ቤተክርስትያን ውስጥ በተለያየ ግዜ በተለያዬ ሁለት አስተማሪዎች የተደረጉ ትምህርቶች ምን ያህል ሰዎች እንደ ተገኙና በምን አይነት የመረዳት ስሜት እንደተማሩ እንዲሁም ምን ያህል ሰዎች የእነዚህን የሁለት ሰዎች ትምህርት በኢንተርኔት እንደተጠቀመ ብናይ እራሳችንን እንታዘበዋለን:: እነዚህ ሁለት የእግዚያብሔር አገልጋዮች አንደኛው ወንጌላዊ ያሬድ ጥላሁንና ሁለተኛው ደግሞ ፓስተር ዳዊት ሞላልኝ ሲሆኑ በእኔ የክርስትና መረዳት ወንጌላዊ ያሬድ በእዚህ ክፍል በተከታታይ ያስተማረው ስለ ክርስትና ዋናው ቁልፍ ስለሆነው ስለ እምነትና ስለዘላለማዊ ህይወት ሲሆን አንባቢዮቼም እናንተም ልትመለከቱት ትችላላችሁ ይህ ስብከት ዩቲዩብ ላይ ከተጫነ እነሆ ወደ 10 ወር ገደማ ሲሆነው ይህንን ጽሁፍ እስከተጻፈበት ሰአት ድረስ 32349 ሰዎች ጎብኝተውታል ይህንን ቪዲዮ ለመጠቀም ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ::

በመቀጠልም የፓስተር ዳዊት ትምህርት ደግሞ የሚያተኩረው ስኬት ላይ ነው የትምህርቱም አብይ ርእስ “ይሳካላቹኋል ይከናወኑላችኋል” የሚል ስጋዊ መገለጥ ያለው ስብከት ሲሆን ይህ ቪዲዮ በዩቲዩብ ላይ ከተጫነ ከወነጌላዊ ያሬድ በሁለት ወር ገደማ ወደፊት ይቀድማል ይህንን ትምህርት ይህንን ጽሁፍ እስከ ወጣበት ሰአት ድረስ 95433 ሰዎች ጎብኝተውታል ይህ ቁጥር ከወንጌላዊ ያሬድ በ3 እጥፍ ብዛት ያለው ክርስትያን ቀልብ ስቧል በተጨማሪም ይህንን ቪዲዮ ለመጠቀም ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ::

አበስ ገበርኩ! ወይም ኢጃኢብ! ያስብላል ስራችንን ለሚያዬ በውጭ ያሉ አለማውያን ሁሉ በክፉ ስራችን ቀንተውብናል:: አሁን አሁንማ አለማውያን በሁለት ተከፍለዋል እነርሱም ጌታጠርቶት ወይም ድንኳን ሰባሪ ክርስቲያን መስሎ በቤተክርስቲያን የሚኖር ተኩላ : እፉኝትና ኩርንችት ክርስትያን እንዲሁም በውጭ እነደፈለገው የሚኖር በስመ ክርስትያን በተለምዶ አለማዊ በመባል ሲታወቁ ይህ በእግዚያብሔር ቤት ያለው ሀሰተኛው ክርስትያን ሁሌም ውሎውና ድርጊቱ በአለም ካለው አለማዊ ስለሚከፋ በአለም ያለው አለማዊ ይህንን በስራው ክፉ የሆነ ክርስትያንን በማየት ብቻ ክርስትያን መሆን እንደሱ ክፍ የሚያደርግ ስለሚመስለው ወደ ቤተክርስትያን ደጃፍ አይቀርብም መጽሐፍ ቅዱስንም አያምንም::
butt-ass-rear-staring-lust-sex-passion-men-ogling-a-woman
በክርስትያን እህቶቻችን ቅጥ ያጣ አለባበስ ስንቶች የእግዚያብሔር ልጆች ጉበታቸው በፍላጻ ተወጋ ስንቶች ከዘላለም ህይወት ወደዘላለም ሞት ሄዱ ስንቶች ከአገልግሎታቸው ተሰናከሉ በክርስትያን እህቶቻችን ባባታችን ልጆች የድፍረት ሀጢያት ጉባኤውን ሁሉ ሞላ:: አሁን ላይ በቤተክርስትያን የሚያተውና የሚሰማው ነገር ሁሉ የቤተክርስትያን የሀጢያት ጽዋ በእርግጥ ሞልቷል ብሎ ለማመን ይቻላል:: ደግሞም አሁን እየመጣ ያለው የእግዚያብሔር የፍርድ ቀን እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ገለጻ ፍርድ የሚጀመረው ከቤተክርስቲያን ነው:: “ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት ተነሥቶ የሚጀመርበት ጊዜ ደርሶአልና፤ አስቀድሞም በእኛ የሚጀመር ከሆነ ለእግዚአብሔር ወንጌል የማይታዘዙ መጨረሻቸው ምን ይሆን?ጻድቅም በጭንቅ የሚድን ከሆነ ዓመፀኛውና ኃጢአተኛው ወዴት ይታይ ዘንድ አለው?” 1 ጴጥ4:17_18
የተወደዳችሁ የክርስቶስ ቤተሰቦች በድፍረት ለመናገር ፈርተናቸው ስንቶች ወገኖቻችን በድፍረት ባለመናገራችን አጠፋናቸው ዛሬ ግን ይህ የድፍረት አለማዊ ልምምድ በእግዚያብሔር ስም ይብቃ ባለፈው ወንድማችን የእግዚያብሔር አገልጋይ ማሙሻ ፋንታ በሀሰተኛው ነቢይ ቡሽሪ (ቡሽራ) በእግዚያብሔር ላይ የተሰራውን ጸያፍ የክህደት ስራ ምክንያት ባስተላለፈው የነቀፌታ ትምህርት በእውነት ስለ ጸያፍ የሀጢያት ስራችን ኡኡ! የሚያስብል ነው:: ነገር ግን ማሙሻ በሚገስጽበት ጉባኤ ሲታይ እንኳን ኡኡ ሊል በሀዘኔታ ከነፈር የመጠጠም ያለ አይመስልም ያለፈው አልፏል የምንልበት ዘመን አይደለም በድፍረት ሀጢያት እየኖርን የምኖርበት ዘመን አይደለም ወደ ትፍታችን እየተመላለስን የምንኖርበት ዘመን አየደለም አሁን ያለንበት ዘመን 11 ኛው ሰአት ጌታን ሲመጣ የምንቀበልበት ሰአት ነው::
Te_Deum_Elizarovo_Guslitsa_8484
በጌታ የተወደዳችሁ ውድ ያባቴ ልጆች እህቶቼና ወንድሞቼ በእዚህ ዘመን በድፍረት ልክልካችንን የሚነግሩን እና የሚገስጹንን አስተማሪዎች በይበልጥ ልንወዳቸው ያስፈልጋል እኔ በበኩሌ ልክልኬን የሚነግሩኝ አስተማሪዎች የመጀመሪያዬ ምርጫ ናቸው:: የተከበራችሁ ውብ የእግዚያብሔ ልጆች እህቶቼ እባካችሁ እባካችሁ ስለእግዚያብሔር ብላችሁ እራሳችሁን ከዛሬ ጀምሮ ካዱ እራሳችሁን ከዛሬ ጀምሮ በራሳችሁ መስቀል እለት እለት ስቀሉ ከሰው ራስ ላይ ወርዳችሁ እራሳችሁን በመስቀሉ ስር ጣሉት ይህንን ብታደርጉ በረከቱ ተቋዳሽ ሁላችንም ነን ስለዚህ የአምልኮ መጀመሪያ ለእግዚያብሔር ቃል ትእዛዝ መገዛት ነው:: ስለዚህም ማንም አየኝ አላየኝ ሳትሉ ሐዋርያው ጳውሎስ እንድታደርጉ ያዘዛችሁን አድርጉ ባታደርጉ ግን በፍርድ ሰአት መልስ ትሰጡበታላችሁ እናንተም የቤተክርስትያን መሪዎችና ሽማግሌዎች ለእግዚያብሔር ቃል ሰለማይታዘዙ በጎች ስላልገሰጽዋቸውና ስላላቃናችዋቸው በፍርድ ቀን መልስ ትሰጣላችሁ:: የተወደዳችሁ የእግዚያብሔር ቤተሰቦች ሀሰተኛ ነቢያቶችና አስተማሪዎች እንዲሁም ሴቶች እህቶቻችን የልብስና የጌጥ የእግዚያብሔር ትእዛዝ ምን እንደሚል በጥንቃቄ ልንመረምር ያስፈልጋል:: የእግዚያብሔርን ትእዛዝ አለማወቅና አለመፈጸም ከፍርድ አያስመልጥም::
bible_sunset
“ ሴት የወንድ ልብስ አትልበስ፥ ወንድም የሴት ልብስ አይልበስ፤ ይህን የሚያደርግ በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ የተጠላ ነውና።”
ዘዳ 22:5
“ ከተልባ እግርና ከበግ ጠጕር በአንድነት የተሠራ ልብስ አትልበስ።” ዘዳ 22:11
“ ሥርዓቴን ጠብቁ። እንስሳህ ከሌላ ዓይነት ጋር አይደባለቅ፤ በእርሻህም ሁለት ዓይነት ዘር አትዝራ፤ ከሁለት ዓይነት ነገር የተሠራ ልብስ አትልበስ።” ዘሌ 19:19
“ እንዲሁም ደግሞ ሴቶች በሚገባ ልብስ ከእፍረትና ራሳቸውን ከመግዛት ጋር ሰውነታቸውን ይሸልሙ፤ እግዚአብሔርን እንፈራለን ለሚሉት ሴቶች እንደሚገባ፥ መልካም በማድረግ እንጂ በሽሩባና በወርቅ ወይም በዕንቍ ወይም ዋጋው እጅግ በከበረ ልብስ አይሸለሙ።” 1ጢሞ2:9_10
“ ለእናንተም ጠጕርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ፥ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ዋጋው እጅግ የከበረ የዋህና ዝግተኛ መንፈስ ያለውን የማይጠፋውን ልብስ ለብሶ የተሰወረ የልብ ሰው ይሁንላችሁ።እንዲህ በቀድሞ ዘመን በእግዚአብሔር ተስፋ ያደረጉት ቅዱሳት ሴቶች ደግሞ ለባሎቻቸው ሲገዙ ተሸልመው ነበርና፤እንዲሁም ሣራ ለአብርሃም። ጌታ ብላ እየጠራችው ታዘዘችለት፤ እናንተም ከሚያስደነግጥ ነገር አንዳች እንኳ ሳትፈሩ መልካም ብታደርጉ ልጆችዋ ናችሁ።” 1ጴጥ 3:3_6
“ራሱን ተከናንቦ የሚጸልይ ወይም ትንቢት የሚናገር ወንድ ሁሉ ራሱን ያዋርዳል።ራስዋን ሳትሸፍን ግን የምትጸልይ ወይም ትንቢት የምትናገር ሴት ሁሉ ራስዋን ታዋርዳለች፤ እንደ ተላጨች ያህል አንድ ነውና።ሴትም ራስዋን ባትሸፍን ጠጉርዋን ደግሞ ትቆረጥ፤ ለሴት ግን ጠጉርዋን መቆረጥ ወይም መላጨት የሚያሳፍር ከሆነ ራስዋን ትሸፍን።ወንድ የእግዚአብሔር ምሳሌና ክብር ስለ ሆነ ራሱን መከናነብ አይገባውም፤ ሴት ግን የወንድ ክብር ናት።” 1 ቆሮ 11: 4_7
“ በጠበበው ደጅ ግቡ፤ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጅ ሰፊ፥ መንገዱም ትልቅ ነውና፥ ወደ እርሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፤ወደ ሕይወት የሚወስደው ደጅ የጠበበ፥ መንገዱም የቀጠነ ነውና፥ የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው።የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ። ከእሾህ ወይን ከኩርንችትስ በለስ ይለቀማልን?እንዲሁ መልካም ዛፍ ሁሉ መልካም ፍሬ ያደርጋል፥ ክፉም ዛፍ ክፉ ፍሬ ያደርጋል።መልካም ዛፍ ክፉ ፍሬ ማፍራት፥ ወይም ክፉ ዛፍ መልካም ፍሬ ማፍራት አይቻለውም።መልካም ፍሬ የማያደርግ ዛፍ ሁሉ ይቆረጣል ወደ እሳትም ይጣላል።ስለዚህም ከፍሬያቸው ታውቋቸዋላችሁ።በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ እንጂ፥ ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።በዚያ ቀን ብዙዎች። ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ በስምህ ትንቢት አልተናገርንምን፥ በስምህስ አጋንንትን አላወጣንምን፥ በስምህስ ብዙ ተአምራትን አላደረግንምን? ይሉኛል። የዚያን ጊዜም። ከቶ አላወቅኋችሁም፤ እናንተ ዓመፀኞች፥ ከእኔ ራቁ ብዬ እመሰክርባቸዋለሁ።” ማቴ 7:13_23
“ ቃሉን ስበክ፥ በጊዜውም አለጊዜውም ጽና፥ ፈጽመህ እየታገሥህና እያስተማርህ፥ ዝለፍና ገሥጽ ምከርም።ሕይወት የሚገኝበትን ትምህርት የማይታገሡበት ዘመን ይመጣልና፤ ነገር ግን ጆሮቻቸውን የሚያሳክክ ስለ ሆነ፥ እንደ ገዛ ምኞታቸው ለራሳቸው አስተማሪዎችን ያከማቻሉ።” 2 ጢሞ4:2_3
“ የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች ተኵላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነቢያት ተጠንቀቁ።” ማቴ 7:15
“ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ይነሣሉና፥ ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ።” ማቴ 24:24
“ኢየሱስም። እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” ዮሐ 14:6
“ ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ።ልጆች ሆይ፥ እናንተ ከእግዚአብሔር ናችሁ አሸንፋችኋቸውማል፥ በዓለም ካለው ይልቅ በእናንተ ያለው ታላቅ ነውና።እነርሱ ከዓለም ናቸው፤ ስለዚህ ከዓለም የሆነውን ይናገራሉ ዓለሙም ይሰማቸዋል።እኛ ከእግዚአብሔር ነን፤ እግዚአብሔርን የሚያውቅ ይሰማናል፤ ከእግዚአብሔር ያልሆነ አይሰማንም። የእውነትን መንፈስና የስሕተትን መንፈስ በዚህ እናውቃለን።” 1 ዮሐ 4:1—6
“ በጾሙ ጊዜ ጸሎታቸውን አልሰማም፤ የሚቃጠለውን መሥዋዕትና የእህሉን ቍርባን ባቀረቡ ጊዜ አልቀበላቸውም፤ በሰይፍና በራብ በቸነፈርም አጠፋቸዋለሁ አለኝ።እኔም። ጌታ እግዚአብሔር ሆይ፥ ወዮ! እነሆ፥ ነቢያት። በእውነት ሰላምን በዚህ ስፍራ እሰጣችኋለሁ እንጂ ሰይፍን አታዩም፥ ራብም አያገኛችሁም ይሉአቸዋል አልሁ።እግዚአብሔርም እንዲህ አለኝ። ነቢያቱ ውሸት በስሜ ትንቢት ይናገራሉ፤ አላክኋቸውም፥ አላዘዝኋቸውም፥ አልተናገርኋቸውም፤ የውሸቱን ራእይ ምዋርትንም ከንቱንም ነገር የልባቸውንም ሽንገላ ይሰብኩላችኋል። ስለዚህ እግዚአብሔር በስሜ ትንቢት ስለሚናገሩ ነቢያት። በዚህች አገር ሰይፍና ራብ አይሆንም ስለሚሉ ስላላክኋቸው ነቢያት እንዲህ ይላል። እነዚያ በሰይፍና በራብ ይጠፋሉ።ትንቢት የሚናገሩላቸውም ሰዎች ከራብና ከሰይፍ የተነሣ በኢየሩሳሌም አደባባይ ይበተናሉ፤ ክፋታቸውንም አፈስስባቸዋለሁ እነርሱንና ሚስቶቻቸውን ወንዶችና ሴቶች ልጆቻቸውንም የሚቀብራቸው አይገኝም።” ኤር 14:12_16
“ በውስጥዋ ያሉ ነቢያት እንደሚጮኽና እንደሚናጠቅ አንበሳ አንድ ሆነው ተማማሉ፤ ነፍሶችን በልተዋል፥ ብልጥግናና ሀብትን ወስደዋል፥ በውስጥዋም መበለቶችን አብዝተዋል። ካህናቶችዋም ሕጌን በድለዋል ቅድሳቴንም አርክሰዋል፤ ቅዱስ በሆነና ቅዱስ ባልሆነ መካከልም አልለዩም፥ በንጹሕና በርኩስ መካከል ያለውን ልዩነት አላስታወቁም፤ ዓይናቸውንም ከሰንበታቴ ሰወሩ እኔም በመካከላቸው ረከስሁ። በውስጥዋ ያሉ አለቆችዋ የስስትን ትርፍ ለማግኘት ሲሉ ደምን ያፈስሱ ዘንድ ነፍሶችንም ያጠፉ ዘንድ እንደሚናጠቁ ተኵላዎች ናቸው። እግዚአብሔርም ሳይናገር ነቢያቶችዋ። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል እያሉ ከንቱን ራእይ በማየት የሐሰትንም ምዋርት ለእነርሱ በማምዋረት ያለ ገለባ በጭቃ ይመርጓቸዋል።” ሕዝ 22:25_28
“ እግዚአብሔር ሕዝቤን ስለሚያስቱ ነቢያት እንዲህ ይላል፤ በጥርሳቸው ሲነክሱ በሰላም ይሰብካሉ፤ በአፋቸው ግን አንዳች በማይሰጥ ሰው ላይ ሰልፍን ያስቡበታል። ስለዚህ ሌሊት ይሆንባችኋል እንጂ ራእይ አይሆንላችሁም፤ ጨለማም ይሆንባችኋል እንጂ አታምዋርቱም፤ ፀሐይም በነቢያት ላይ ትገባለች፥ ቀኑም ይጠቁርባቸዋል። ከእግዚአብሔርም ዘንድ መልስ የለምና ባለ ራእዩቹ ያፍራሉ፥ ምዋርተኞችም ይዋረዳሉ፤ ሁሉም ከንፈራቸውን ይሸፍናሉ። እኔ ግን በደሉን ለያዕቆብ፥ ኃጢአቱንም ለእስራኤል እነግር ዘንድ በእግዚአብሔር መንፈስ ኃይልንና ፍርድን ብርታትንም ተሞልቻለሁ። ፍርድን የምትጠሉ ቅን ነገርንም ሁሉ የምታጣምሙ እናንተ የያዕቆብ ቤት አለቆችና የእስራኤል ቤት ገዦች ሆይ፥ እባካችሁ ይህን ስሙ። ጽዮንን በደም፥ ኢየሩሳሌምንም በኃጢአት ይሠራሉ።አለቆችዋ በጉቦ ይፈርዳሉ፥ ካህናቶችዋም በዋጋ ያስተምራሉ፥ ነቢያቶችዋም በገንዘብ ያምዋርታሉ፤ ከዚህም ጋር። እግዚአብሔር በመካከላችን አይደለምን? ክፉ ነገር ምንም አይመጣብንም እያሉ በእግዚአብሔር ይታመናሉ።” ሚልኪያስ 3:5_11
“ መጋደላችን ከደምና ከሥጋ ጋር አይደለምና፥ ከአለቆችና ከሥልጣናት ጋር ከዚህም ከጨለማ ዓለም ገዦች ጋር በሰማያዊም ስፍራ ካለ ከክፋት መንፈሳውያን ሠራዊት ጋር ነው እንጂ።ስለዚህ በክፉው ቀን ለመቃወም፥ ሁሉንም ፈጽማችሁ ለመቆም እንድትችሉ የእግዚአብሔርን ዕቃ ጦር ሁሉ አንሡ። እንግዲህ ወገባችሁን በእውነት ታጥቃችሁ፥ የጽድቅንም ጥሩር ለብሳችሁ፥ በሰላም ወንጌልም በመዘጋጀት እግሮቻችሁ ተጫምተው ቁሙ፤በሁሉም ላይ ጨምራችሁ የሚንበለበሉትን የክፉውን ፍላጻዎች ሁሉ ልታጠፉ የምትችሉበትን የእምነትን ጋሻ አንሡ፤የመዳንንም ራስ ቁር የመንፈስንም ሰይፍ ያዙ እርሱም የእግዚአብሔር ቃል ነው።በጸሎትና በልመናም ሁሉ ዘወትር በመንፈስ ጸልዩ፤ በዚህም አሳብ ስለ ቅዱሳን ሁሉ እየለመናችሁ በመጽናት ሁሉ ትጉ::” ኤፌ6:12_18
“ ጕበኞቹ ዕውሮች ናቸው፥ ሁሉ ያለ እውቀት ናቸው፤ ሁሉም ዲዳ የሆኑ ውሾች ናቸው ይጮኹም ዘንድ አይችሉም፤ ሕልምን ያልማሉ፤ ይተኛሉ፤ ማንቀላፋትንም ይወድዳሉ።መብል ወዳጆች ከቶ የማይጠግቡ ውሾች ናቸው፥ እነርሱም ያስተውሉ ዘንድ የማይችሉ እረኞች ናቸው፤ ሁሉ ወደ መንገዳቸው፥ ከፊተኛው እስከ ኋለኛው ድረስ ሁሉ፥ እያንዳንዳቸው ወደ ጥቅማቸው ዘወር ብለዋል።” ኢሳ 56:10_11
“ ነገር ግን ሐሰተኞች ነቢያት ደግሞ በሕዝቡ መካከል ነበሩ እንዲሁም በመካከላችሁ ደግሞ ሐሰተኞች አስተማሪዎች ይሆናሉ፤ እነርሱም የዋጃቸውን ጌታ እንኳ ክደው የሚፈጥንን ጥፋት በራሳቸው ላይ እየሳቡ የሚያጠፋ ኑፋቄን አሹልከው ያገባሉ፤ብዙዎችም በመዳራታቸው ይከተሉአቸዋል በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል። ገንዘብንም በመመኘት በተፈጠረ ነገር ይረቡባችኋል፤ ፍርዳቸውም ከጥንት ጀምሮ አይዘገይም ጥፋታቸውም አያንቀላፋም።እግዚአብሔር ኃጢአትን ላደረጉ መላእክት ሳይራራላቸው ወደ ገሃነም ጥሎ በጨለማ ጉድጓድ ለፍርድ ሊጠበቁ አሳልፎ ከሰጣቸው፥ለቀደመውም ዓለም ሳይራራ ከሌሎች ሰባት ጋር ጽድቅን የሚሰብከውን ኖኅን አድኖ በኃጢአተኞች ዓለም ላይ የጥፋትን ውኃ ካወረደ፥ኃጢአትንም ያደርጉ ዘንድ ላሉት ምሳሌ አድርጎ ከተማዎችን ሰዶምንና ገሞራን አመድ እስኪሆኑ ድረስ አቃጥሎና ገልብጦ ከፈረደባቸው፥ጻድቅ ሎጥም በመካከላቸው ሲኖር እያየና እየሰማ ዕለት ዕለት በዓመፀኛ ሥራቸው ጻድቅ ነፍሱን አስጨንቆ ነበርና በዓመፀኞች ሴሰኛ ኑሮ የተገፋውን ያን ጻድቅ ካዳነ፥ ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመልኩትን ከፈተና እንዴት እንዲያድን፥ በደለኞችንም ይልቁንም በርኵስ ምኞት የሥጋን ፍትወት እየተከተሉ የሚመላለሱትን ጌትነትንም የሚንቁትን እየቀጣቸው ለፍርድ ቀን እንዴት እንዲጠብቅ ያውቃል። ደፋሮችና ኵሩዎች ሆነው ሥልጣን ያላቸውን ሲሳደቡ አይንቀጠቀጡም፤ዳሩ ግን መላእክት በኃይልና በብርታት ከእነርሱ ይልቅ ምንም ቢበልጡ በጌታ ፊት በእነርሱ ላይ የስድብን ፍርድ አያመጡም።እነዚህ ግን ለመጠመድና ለመጥፋት በፍጥረታቸው እንደ ተወለዱ አእምሮ እንደ ሌላቸው እንስሶች ሆነው፥ በማያውቁት ነገር እየተሳደቡ በጥፋታቸው ይጠፋሉ፤የዓመፃቸውን ደመወዝ ይቀበላሉ። በቀን ሲዘፍኑ እንደ ተድላ ይቆጥሩታል፤ ነውረኞችና ርኵሳን ሆነው ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣ ይዘፍናሉ፤ምንዝር የሞላባቸው ኃጢአትንም የማይተዉ ዓይኖች አሉአቸው፤ የማይጸኑትን ነፍሳት ያታልላሉ፤ መመኘትን የለመደ ልብ አላቸው፤ የተረገሙ ናቸው።ቅንን መንገድ ትተው ተሳሳቱ፤ የባሶርን ልጅ የበለዓምን መንገድ ተከተሉ፤ እርሱ የዓመፃን ደመወዝ ወደደ፥ነገር ግን ስለ መተላለፉ ተዘለፈ፤ ቃል የሌለው አህያ በሰው ቃል ተናግሮ የነቢዩን እብድነት አገደ።ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው እነዚህ ውኃ የሌለባቸው ምንጮች በዐውሎ ነፋስም የተነዱ ደመናዎች ናቸው።ከንቱና ከመጠን ይልቅ ታላቅ የሆነውን ቃል ይናገራሉና፥ በስሕተትም ከሚኖሩት አሁን የሚያመልጡትን በሥጋ ሴሰኛ ምኞት ያታልላሉ።ራሳቸው የጥፋት ባሪያዎች ሆነው። አርነት ትወጣላችሁ እያሉ ተስፋ ይሰጡአቸዋል፤ ሰው ለተሸነፈበት ለእርሱ ተገዝቶ ባሪያ ነውና።በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እውቀት ከዓለም ርኵሰት ካመለጡ በኋላ ዳግመኛ በእርስዋ ተጠላልፈው የተሸነፉ ቢሆኑ፥ ከፊተኛው ኑሮአቸው ይልቅ የኋለኛው የባሰ ሆኖባቸዋል።አውቀዋት ከተሰጣቸው ከቅድስት ትእዛዝ ከሚመለሱ የጽድቅን መንገድ ባላወቋት በተሻላቸው ነበርና።ውሻ ወደ ትፋቱ ይመለሳል፥ ደግሞ። የታጠበች እርያ በጭቃ ለመንከባለል ትመለሳለች እንደሚባል እውነተኞች ምሳሌዎች ሆኖባቸዋል::” 2 ጴጥ 2
“ ኢሳይያስ ስለ እናንተ ስለ ግብዞች። ይህ ሕዝብ በከንፈሩ ያከብረኛል ልቡ ግን ከእኔ በጣም የራቀ ነው፤የሰውም ሥርዓት የሆነ ትምህርት እያስተማሩ በከንቱ ያመልኩኛል ተብሎ እንደ ተጻፈ በእውነት ትንቢት ተናገረ። የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትታችሁ ጽዋን ማድጋንም እንደ ማጠብ የሰውን ወግ ትጠብቃላችሁ፥ ይህንም የመሰለ ብዙ ሌላ ነገር ታደርጋላችሁ።እንዲህም አላቸው። ወጋችሁን ትጠብቁ ዘንድ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ እጅግ ንቃችኋል። ” ማር 7:6—9
“ ያሳታቸውም ዲያብሎስ አውሬውና ሐሰተኛው ነቢይ ወዳሉበት ወደ እሳቱና ወደ ዲኑ ባሕር ተጣለ፥ ለዘላለምም እስከ ዘላለም ቀንና ሌሊት ይሣቀያሉ።” ራዕ 20:10
“ በልሳን የሚናገር ቢኖር ሁለት ወይም ቢበዛ ሦስት ሆነው በተራቸው ይናገሩ አንዱም ይተርጉም፤የሚተረጉም ባይኖር ግን በማኅበር መካከል ዝም ይበልና ለራሱና ለእግዚአብሔር ይናገር። ነቢያትም ሁለት ወይም ሦስት ሆነው ይናገሩ ሌሎችም ይለዩአቸው፤በዚያ ለሚቀመጥ ለሌላ ግን አንድ ነገር ቢገለጥለት ፊተኛው ዝም ይበል።ሁሉም እንዲማሩ ሁሉም እንዲመከሩ ሁላችሁ በእያንዳንዳችሁ ትንቢት ልትናገሩ ትችላላችሁ።የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ::” 1 ቆሮ 14: 27_32
“ ከወንድሞቻቸው መካከል እንደ አንተ ያለ ነቢይ አስነሣላቸዋለሁ፤ ቃሌንም በአፉ አደርጋለሁ፥ ያዘዝሁትንም ቃል ሁሉ ይነግራቸዋል፤በስሜም የሚናገረውን ቃሌን የማይሰማውን ሰው እኔ እበቀልለታለሁ።ነገር ግን ይናገር ዘንድ ያላዘዝሁትን በስሜ በድፍረት የሚናገር ወይም በሌላ አማልክት ስም የሚናገር ነቢይ፥ እርሱ ይገደል።በልብህም። እግዚአብሔር ያልተናገውን ቃል እናውቅ ዘንድ እንዴት ይቻለናል? ብትል፥ነቢዩ በእግዚአብሔር ስም በተናገረ ጊዜ የተናገረው ነገር ባይሆን ባይመጣም፥ ያ ነገር እግዚአብሔር ያልተናገረው ነው፤ ነቢዩ በድፍረቱ ተናግሮታል እርሱን አትፍራው። ” ዘዳ 18: 18_22
ሕዝቃኤል ምዕራፍ 13።
“ የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። የሰው ልጅ ሆይ፥ ትንቢት በሚናገሩ በእስራኤል ነቢያት ላይ ትንቢት ተናገር፥ ከገዛ ልባቸውም ትንቢት የሚናገሩትን። የእግዚአብሔርን ቃል ስሙ በላቸው፤ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ምንምን ሳያዩ የገዛ መንፈሳቸውን ለሚከተሉ ለሰነፎች ነቢያት ወዮላቸው! እስራኤል ሆይ፥ ነቢያትህ በምድረ በዳ እንደሚኖሩ ቀበሮች ናቸው። ወደ ተሰበረው ቅጥር አልወጣችሁም፥ በእግዚአብሔርም ቀን በሰልፍ ትቆሙ ዘንድ ለእስራኤል ቤት ቅጥር አልሠራችሁም። እግዚአብሔር ሳይልካቸው። እግዚአብሔር ይላል የሚሉ ሰዎች ከንቱ ነገርንና ውሸተኛ ምዋርትን አይተዋል፤ ቃሉም ይጠና ዘንድ ተስፋ አስደርገዋል። እኔም ሳልናገር። እግዚአብሔር እንዲህ ብሎአል ስትሉ፥ ከንቱ ራእይን ያያችሁ ውሸተኛንም ምዋርት የተናገራችሁ አይደላችሁምን? ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ከንቱ ነገርን ስለ ተናገራችሁ ውሸተኛ ራእይንም ስላያችሁ፥ ስለዚህ፥ እነሆ፥ እኔ በእናንተ ላይ ነኝ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። እጄም ከንቱ ራእይን በሚያዩ፥ በውሸትም በሚያምዋርቱ ነቢያት ላይ ትሆናለች፤ እነርሱም በሕዝቤ ማኅበር ውስጥ አይገኙም፥ በእስራኤልም ቤት መጽሐፍ አይጻፉም፥ ወደ እስራኤልም ምድር አይገቡም፤ እኔም ጌታ እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ያውቃሉ። ሰላም ሳይኖር። ሰላም እያሉ ሕዝቤን አታልለዋልና፤ አንዱም ሰው ቅጥር ሲሠራ፥ እነሆ፥ ገለባ በሌለበት ጭቃ ይመርጉታልና ገለባ በሌለበት ጭቃ ለሚመርጉት ሰዎች። ይወድቃል በላቸው። የሚያሰጥም ዝናብ ይዘንባል፥ ታላቅም የበረዶ ድንጋይ ይወድቃል፥ ዐውሎ ነፋስም ይሰነጣጥቀዋል። እነሆ፥ ግንቡ በወደቀ ጊዜ። የመረጋችሁት ጭቃ ወዴት አለ? አይሉአችሁምን? ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። በመዓቴ በዐውሎ ነፋስ እሰነጣጥቀዋለሁ፥ ያጠፋውም ዘንድ በቍጣዬ የሚያሰጥም ዝናብ፥ በመዓቴም ታላቅ የበረዶ ድንጋይ ይወርዳል። ገለባም በሌለበት ጭቃ የመረጋችሁትን ቅጥር አፈርሳለሁ ወደ ምድርም እጥለዋለሁ፥ መሠረቱም ይታያል። እርሱም ይናዳል በመካከሉም ትጠፋላችሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። መዓቴንም በግንቡ ላይ ገለባም በሌለበት ጭቃ በመረጉት ላይ እፈጽማለሁ፤ እኔም። ግንቡና መራጊዎቹ የሉም እላችኋለሁ። እነርሱም ስለ ኢየሩሳሌም ትንቢት የሚናገሩ የሰላምን ራእይ የሚያዩላት የእስራኤል ነቢያት ናቸው፥ ሰላምም የለም፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር። አንተም፥ የሰው ልጅ ሆይ፥ ከገዛ ልባቸው ትንቢት በሚናገሩ በሕዝብህ ሴቶች ልጆች ላይ ፊትህን አድርግ፤ ትንቢትም ተናገርባቸው፥ እንዲህም በል። ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ነፍስን ለማጥመድ ለእጅ ድጋፍ ሁሉ መከዳ ለሚሰፉ ለሰውም ሁሉ ራስ እንደ እየቁመቱ ሽፋን ለሚሠሩ ሴቶች ወዮላቸው! የሕዝቤንም ነፍስ ብታጠምዱ በውኑ ነፍሳችሁን ታድናላችሁን? ውሸታችሁን ለሚሰሙት ሕዝቤ እየዋሻችሁ ሞት የማይገባቸውን ነፍሳት ትገድሉ ዘንድ በሕይወትም መኖር የማይገባቸውን ነፍሳት በሕይወት ታኖሩ ዘንድ ስለ ጭብጥ ገብስና ስለ ቍራሽ እንጀራ በሕዝቤ ዘንድ አርክሳችሁኛል። ስለዚህ ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ እኔ ነፍሳትን እንደ ወፍ በምታጠምዱባት በመከዳችሁ ላይ ነኝ፥ ከክንዳችሁም ወስጄ እቀድዳታለሁ፥ እንደ ወፍም የምታጠምዱአቸውን ነፍሳት እለቅቃለሁ። ሽፋኖቻችሁን ደግሞ እቀድዳለሁ ሕዝቤንም ከእጃችሁ አድናለሁ፥ ከዚያም ወዲያ በእጃችሁ ለመታደን አይሆኑም፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ። እኔም ያላሳዘንሁትን የጻድቁን ልብ በውሸት አሳዝናችኋልና፥ በሕይወትም ይኖር ዘንድ ከክፉ መንገድ እንዳይመለስ የኃጢአተኛውን እጅ አበርትታችኋልና ስለዚህ ከንቱን ራእይ እንግዲህ አታዩም ምዋርትንም አታምዋርቱም፥ ሕዝቤንም ከእጃችሁ አድናለሁ፤ እኔም እግዚአብሔር እንደ ሆንሁ ታውቃላችሁ።”
ኤርሚያስ ምዕራፍ 23
“ የማሰማርያዬን በጎች ለሚያጠፉና ለሚበትኑ እረኞች ወዮላቸው! ይላል እግዚአብሔር።ስለዚህ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር ሕዝቤን ስለሚጠብቁ እረኞች እንዲህ ይላል። በጎቼን በትናችኋል አባርራችኋቸውማል አልጐበኛችኋቸውምም፤ እነሆ፥ የሥራችሁን ክፋት እጐበኝባችኋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።የመንጋዬም ቅሬታ ካባረርኋቸው ምድር ሁሉ ወደ በረታቸው ሰብሰቤ እመልሳቸዋለሁ፤ እነርሱም ያፈራሉ ይበዙማል።የሚጠብቋቸውን እረኞች አስነሣላቸዋለሁ፥ ዳግመኛም አይፈሩምና አይደነግጡም፥ ከእነሱም አንድ አይጐድልም፥ ይላል እግዚአብሔር።እነሆ፥ ለዳዊት ጻድቅ ቍጥቋጥ የማስነሣበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፥ እርሱም እንደ ንጉሥ ይነግሣል፥ ይከናወንለታልም፥ በምድርም ፍርድንና ጽድቅን ያደርጋል።በዘመኑም ይሁዳ ይድናል እስራኤልም ተዘልሎ ይቀመጣል፥ የሚጠራበትም ስም። እግዚአብሔር ጽድቃችን ተብሎ ነው።ስለዚህ፥ እነሆ። የእስራኤልን ልጆች ከግብጽ ምድር ያወጣ ሕያው እግዚአብሔርን! ዳግመኛ የማይባልበት ዘመን ይመጣል፥ ይላል እግዚአብሔር፤ነገር ግን። የእስራኤልን ቤት ዘር ከሰሜን አገርና ካሰደድኋቸውም አገር ሁሉ ያወጣና የመራ ሕያው እግዚአብሔርን! ይባላል፤ በምድራቸውም ይቀመጣሉ።ስለ ነቢያት፤ ልቤ በውስጤ ተሰብሮአል አጥንቶቼም ሁሉ ታውከዋል፤ ከእግዚአብሔር የተነሣ ከቅዱስ ቃሉም የተነሣ የወይን ጠጅ እንዳሸነፈው እንደ ሰካራም ሰው ሆኛለሁ።ምድር ከአመንዝሮች ተሞልታለችና፥ ከመርገምም የተነሣ ምድር አልቅሳለች፤ የምድረ በዳ ማሰማርያ ደርቆአል፤ አካሄዳቸው ክፉ ነው፥ ብርታታቸውም ቅን አይደለም።ነቢዩና ካህኑም ረክሰዋልና፥ በቤቴም ውስጥ ክፋታቸውን አግኝቻለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር።ስለዚህ መንገዳቸው በጨለማ እንዳለች እንደ ድጥ ስፍራ ትሆንባቸዋለች፥ እነርሱም ፍግምግም ብለው ይወድቁባታል፤ እኔም በምጐበኛቸው ዓመት ክፉ ነገርን አመጣባቸዋለሁና፥ ይላል እግዚአብሔር።በሰማርያ ነቢያት ላይ ስንፍናን አይቻለሁ፤ በበኣል ትንቢት ይናገሩ ነበር፥ ሕዝቤንም እስራኤል ያስቱ ነበር። በኢየሩሳሌምም ነቢያት ላይ የሚያስደነግጥን ነገር አይቻለሁ፤ ያመነዝራሉ በሐሰትም ይሄዳሉ፤ ማንም ከክፋቱ እንዳይመለስ የክፉ አድራጊዎችን እጅ ያበረታሉ፤ ሁሉም እንደ ሰዶም የሚኖሩባትም እንደ ገሞራ ሆኑብኝ።ስለዚህ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እነሆ፥ ከኢየሩሳሌም ነቢያት ዘንድ ርኵሰት በምድር ሁሉ ላይ ወጥቶአልና እሬትን አበላቸዋለሁ የሐሞትንም ውኃ አጠጣቸዋለሁ።የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ትንቢት የሚናገሩላችሁን የነቢያትን ቃል አትሰሙ፤ ከንቱነትን ያስተምሩአችኋል፤ ከእግዚአብሔር አፍ ሳይሆን ከገዛ ልባቸው የወጣውን ራእይ ይናገራሉ።ለሚንቁኝ ሁልጊዜ። እግዚአብሔር። ሰላም ይሆንላችኋል ብሎአል ይላሉ፤ በልቡም እልከኝነት ለሚሄድ ሁሉ። ክፉ ነገር አያገኛችሁም ይላሉ።ቃሉን ያይና ይሰማ ዘንድ በእግዚአብሔር ምክር የቆመ ማን ነውና? ቃሉንስ ያደመጠ የሰማስ ማን ነው?እነሆ፥ የእግዚአብሔር ዐውሎ ነፋስ፥ እርሱም ቍጣው፥ የሚያገለባብጥ ዐውሎ ነፍስ ወጥቶአል፤ የዓመፀኞችን ራስ ይገለባብጣል።የእግዚአብሔር ቍጣ የልቡን አሳብ ሠርቶ እስኪፈጽም ድረስ አይመለስም፤ በኋለኛው ዘመን ፈጽማችሁ ታስተውሉታላችሁ።እኔ ሳልልካቸው እነዚህ ነቢያት ሮጡ፤ እኔም ሳልነግራቸው ትንቢትን ተናገሩ።በምክሬ ግን ቢቆሙ ኖሮ፥ ለሕዝቤ ቃሌን ባሰሙ ነበር፥ ከክፉም መንገዳቸው ከሥራቸውም ክፋት በመለሱአቸው ነበር።እኔ የቅርብ አምላክ ነኝ እንጂ የሩቅ አምላክ አይደለሁም።ሰው በስውር ቢሸሸግ፥ እኔ አላየውምን? ሰማይንና ምድርንስ የሞላሁ እኔ አይደለሁምን? ይላል እግዚአብሔር። አለምሁ አለምሁ እያሉ በስሜ ሐሰትን የሚናገሩትን የነቢያትን ነገር ሰምቻለሁ።ትንቢትን በሐሰት በሚናገሩ፥ የልባቸውንም ሽንገላ በሚናገሩ በነቢያት ልብ ይህ የሚሆነው እስከ መቼ ነው?አባቶቻቸው ስለ በኣል ስሜን እንደ ረሱ፥ እያንዳንዱ ለባልንጀራው በሚናገራት ሕልማቸው ሕዝቤ ስሜን ለማስረሳት ያስባሉ። የሚያልም ነቢይ ሕልምን ይናገር፤ ቃሌም ያለበት ቃሌን በእውነት ይናገር። ገለባ ከስንዴ ጋር ምን አለው?በውኑ ቃሌ እንደ እሳት፥ ድንጋዩንም እንደሚያደቅቅ መዶሻ አይደለችምን? ይላል እግዚአብሔር። ስለዚህ፥ እነሆ፥ እያንዳንዱ ከባልንጀራው ዘንድ ቃሌን በሚሰርቁ ነቢያት ላይ ነኝ፥ ይላል እግዚአብሔር።እነሆ፥ ከምላሳቸው ትንቢትን አውጥተው። እርሱ ይላል በሚሉ ነቢያት ላይ ነኝ፥ ይላል እግዚአብሔር።እነሆ፥ ሐሰትን በሚያልሙ በሚናገሩም በሐሰታቸውና በድፍረታቸውም ሕዝቤን በሚያስቱ በነቢያት ላይ ነኝ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እኔም አልላክኋቸውም አላዘዝኋቸውምም ለእነዚህም ሕዝብ በማናቸውም አይረቡአቸውም፥ ይላል እግዚአብሔር።ይህ ሕዝብ ወይም ነቢይ ወይም ካህን። የእግዚአብሔር ሸክም ምንድር ነው? ብሎ ቢጠይቅህ፥ አንተ። ሸክሙ እናንተ ናችሁ፥ እጥላችሁማለህ፥ ይላል እግዚአብሔር ትላቸዋለህ።የእግዚአብሔር ሸክም የሚለውን ነቢይንና ካህንን ሕዝቡንም ያን ሰውና ቤቱን እቀጣለሁ።አንዱም አንዱ ለባልንጀራው፥ አንዱም አንዱ ለወንድሙ እንዲህ ይበል። እግዚአብሔር የመለሰው ምንድር ነው? እግዚአብሔርስ ምን ነገር ተናገረ?ለሰው ሁሉ ቃል ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ይሆንበታልና የእግዚአብሔር ሸክም ብላችሁ ከእንግዲህ ወዲህ አትጥሩ፤ የሠራዊትን ጌታ የአምላካችንን የእግዚአብሔርን የሕያውን አምላክ ቃል ለውጣችኋልና።ለነቢዩ። እግዚአብሔር ምን መለሰልህ? እግዚአብሔርስ የተናገረው ምንድር ነው? ትላለህ።ነገር ግን። የእግዚአብሔር ሸክም ብትሉ፥ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። እኔ። የእግዚአብሔር ሸክም አትበሉ ብዬ ልኬባችኋለሁና፥ እናንተም ይህን ቃል።የእግዚአብሔር ሸክም ብላችኋልና ስለዚህ፥ እነሆ፥ ፈጽሜ እረሳችኋለሁ እናንተንም ለእናንተና ለአባቶቻችሁም የሰጠኋትን ከተማ ከፊቴ እጥላለሁ።የዘላለምንም ስድብ ከቶም ተረስቶ የማይጠፋውን የዘላለምን እፍረት አመጣባችኋለሁ።”
ዘካሪያስ ምዕራፍ 13።
“ በዚያ ቀን ለዳዊት ቤትና በኢየሩሳሌም ለሚኖሩ ከኃጢአትና ከርኵሰት የሚያነጻ ምንጭ ይከፈታል። በዚያ ቀን፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፥ የጣዖታትን ስም ከምድር አጠፋለሁ፥ ከዚያም በኋላ አይታሰቡም፤ ደግሞም ሐሰተኞችን ነቢያትና ርኩስ መንፈስን ከምድር ላይ አስወግዳለሁ። ማንም ደግሞ ትንቢት ቢናገር የወለዱት አባቱና እናቱ። አንተ በእግዚአብሔር ስም ሐሰትን ተናግረሃልና በሕይወት አትኖርም ይሉታል፤ ትንቢትንም ሲናገር የወለዱት አባቱና እናቱ ይወጉታል። በዚያም ቀን ነቢያቱ ሁሉ ትንቢትን ሲናገሩ እያንዳንዱ ስለ ራእዩ ያፍራል፤ ያታልሉም ዘንድ የማቅ ልብስ አይለብሱም። እርሱ ግን። ከታናሽነቴ ጀምሮ ባሪያ ሆኜ ነበርሁና ገበሬ ሰው ነኝ እንጂ ነቢይ አይደለሁም ይላል። ሰውም። ይህ በእጅህ መካከል ያለ ቍስል ምንድር ነው? ይለዋል። እርሱም። በወዳጆቼ ቤት የቈሰልሁት ቍስል ነው ይላል። ሰይፍ ሆይ፥ ባልንጀራዬ በሆነው ሰው በእረኛዬ ላይ ንቃ፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፤ እረኛውን ምታ፥ በጎቹም ይበተናሉ፤ እጄንም በታናናሾች ላይ እመልሳለሁ።በምድርም ሁሉ ላይ ሁለት ክፍል ተቈርጠው ይሞታሉ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ሦስተኛውም ክፍል በእርስዋ ውስጥ ይቀራል። ሦስተኛውንም ክፍል ወደ እሳት አገባለሁ፥ ብርም እንደሚነጥር አነጥራቸዋለሁ፥ ወርቅም እንደሚፈተን እፈትናቸዋለሁ፤ እነርሱም ስሜን ይጠራሉ፥ እኔም እሰማቸዋለሁ፤ እኔም። ይህ ሕዝቤ ነው እላለሁ፤ እርሱም። እግዚአብሔር አምላኬ ነው ይላል።”
“ሥራህንና ድካምህን ትዕግሥትህንም አውቃለሁ፤ ክፉዎችንም ልትታገሥ እንዳትችል፥ እንዲሁም ሳይሆኑ። ሐዋርያት ነን የሚሉቱን መርምረህ ሐሰተኞች ሆነው እንዳገኘሃቸው አውቃለሁ፤ታግሠህማል፥ ስለ ስሜም ብለህ ጸንተህ አልደከምህም።” ራዕ 2:2_3
“ ነቢያት በሐሰት ትንቢት ይናገራሉ፥ ካህናትም በእነዚህ እጅ ይገዛሉ፥ ሕዝቤም እንዲህ ያለውን ነገር ይወድዳሉ፤ በፍጻሜውስ ምን ታደርጋላችሁ?” ኤር 5:31
“ እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜአቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።” 2 ቆሮ 11:13_15
“ የሐሰተኞችን ምልክት ከንቱ አደርጋለሁ፥ ምዋርተኞችንም አሳብዳለሁ፥ ጥበበኞቹንም ወደ ኋላ እመልሳለሁ እውቀታቸውንም ስንፍና አደርጋለሁ::” ኢሳ 44:25
“አክዓብም ኤልያስን ባየው ጊዜ። እስራኤልን የምትገለባብጥ አንተ ነህን? አለው። ኤልያስም። እስራኤልን የምትገለባብጡ፥ የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ትታችሁ በኣሊምን የተከተላችሁ፥ አንተና የአባትህ ቤት ናችሁ እንጂ እኔ አይደለሁም። አሁንም ልከህ እስራኤልን ሁሉ፥ በኤልዛቤልም ማዕድ የሚበሉትን አራት መቶ አምሳ የበኣልን ነቢያት፥ አራት መቶም የማምለኪያ ዐፀድን ነቢያት ወደ እኔ ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ሰብስብ አለ። አክዓብም ወደ እስራኤል ልጆች ሁሉ ልኮ ነቢያቱን ሁሉ ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ሰበሰበ። ኤልያስም ወደ ሕዝቡ ሁሉ ቀርቦ። እስከ መቼ ድረስ በሁለት አሳብ ታነክሳላችሁ? እግዚአብሔር አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ፤ በኣል ግን አምላክ ቢሆን እርሱን ተከተሉ አለ። ሕዝቡም አንዲት ቃል አልመለሱለትም። ኤልያስም ሕዝቡን አለ። ከእግዚአብሔር ነቢያት እኔ ብቻ ቀርቻለሁ፤ የበኣል ነቢያት ግን አራት መቶ አምሳ ሰዎች ናቸው። ሁለት ወይፈኖች ይሰጡን፤ እነርሱም አንድ ወይፈን ይምረጡ፥ እየብልቱም ይቍረጡት፥ በእንጨትም ላይ ያኑሩት፥ በበታቹም እሳት አይጨምሩ፤ እኔም ሁለተኛውን ወይፈን አዘጋጃለሁ፥ በእንጨቱም ላይ አኖረዋለሁ፥ በበታቹም እሳት አልጨምርም። እናንተም የአምላካችሁን ስም ጥሩ፥ እኔም የእግዚአብሔርን ስም እጠራለሁ፤ ሰምቶም በእሳት የሚመልስ አምላክ፥ እርሱ አምላክ ይሁን። ሕዝቡም ሁሉ። ይህ ነገር መልካም ነው ብለው መለሱ። ኤልያስም የበኣልን ነቢያት። እናንተ ብዙዎች ናችሁና አስቀድማችሁ አንድ ወይፈን ምረጡና አዘጋጁ፤ የአምላካችሁንም ስም ጥሩ፥ በበታችሁም እሳት አትጨምሩ አላቸው። ወይፈኑንም ወስደው አዘጋጁ፥ ከጠዋትም እስከ ቀትር ድረስ። በኣል ሆይ፥ ስማን እያሉ የበኣልን ስም ጠሩ። ድምፅም አልነበረም፥ የሚመልስም አልነበረም፤ በሠሩትም መሠዊያ ዙሪያ እያነከሱ ያሸበሽቡ ነበር። በቀትርም ጊዜ ኤልያስ። አምላክ ነውና በታላቅ ቃል ጩኹ፤ ምናልባት አሳብ ይዞታል፥ ወይም ፈቀቅ ብሎአል፥ ወይም ወደ መንገድ ሄዶአል፥ ወይም ተኝቶ እንደ ሆነ መቀስቀስ ያስፈልገዋል እያለ አላገጠባቸው። በታላቅም ቃል ይጮኹ፥ እንደ ልማዳቸውም ደማቸው እስኪፈስስ ድረስ ገላቸውን በካራና በቀጭኔ ይብዋጭሩ ነበር። ቀትርም ካለፈ በኋላ መሥዋዕተ ሠርክ እስኪደርስ ትንቢት ይናገሩ ነበር፤ ድምፅም አልነበረም፥ የሚመልስና የሚያደምጥም አልነበረም። ኤልያስም ሕዝቡን ሁሉ። ወደ እኔ ቅረቡ አላቸው። ሕዝቡም ሁሉ ወደ እርሱ ቀረቡ። ፈርሶ የነበረውንም የእግዚአብሔርን መሠዊያ አበጀ። ኤልያስም። ስምህ እስራኤል ይሆናል የሚል የእግዚአብሔር ቃል እንደ ደረሰለት እንደ ያዕቆብ ልጆች ነገድ ቍጥር አሥራ ሁለቱን ድንጋዮች ወሰደ። ከድንጋዮችም ለእግዚአብሔር ስም መሠዊያ ሠራ፤ በመሠዊያውም ዙሪያ ሁለት መስፈሪያ እህል የሚያዝ ጕድጓድ ቈፈረ። እንጨቱንም በተርታ አደረገ፥ ወይፈኑንም በብልት በብልቱ ቈረጠ፥ በእንጨቱም ላይ አኖረና። አራት ጋን ውኃ ሙሉ በሚቃጠለው መሥዋዕትና በእንጨቱ ላይ አፍስሱ አሉ። ደግሞም። ድገሙ አለ፤ እነርሱም ደገሙ። እርሱም። ሦስተኛ አድርጉ አለ፤ ሦስተኛም አደረጉ። ውኃውም በመሠዊያው ዙሪያ ፈሰሰ፤ ደግሞም ጕድጓዱን በውኃ ሞላው።መሥዋዕተ ሠርክ በሚቀርብበት ጊዜ ነቢዩ ኤልያስ ቀርቦ። አቤቱ፥ የአብርሃምና የይስሐቅ የእስራኤልም አምላክ ሆይ፥ አንተ በእስራኤል ላይ አምላክ እንደ ሆንህ፥ እኔም ባሪያህ እንደ ሆንሁ፥ ይህንም ሁሉ በቃልህ እንዳደረግሁ ዛሬ ይገለጥ።አንተ፥ አቤቱ፥ አምላክ እንደ ሆንህ፥ ልባቸውንም ደግሞ እንደ መለስህ ይህ ሕዝብ ያውቅ ዘንድ ስማኝ፥ አቤቱ፥ ስማኝ አለ።የእግዚአብሔርም እሳት ወደቀች፥ የሚቃጠለውን መሥዋዕቱንም እንጨቱንም ድንጋዮቹንም አፈሩንም በላች፥ በጕድጓዱም ውስጥ ያለውን ውኃ ላሰች።ሕዝቡም ሁሉ ያንን ባዩ ጊዜ በግምባራቸው ተደፍተው። እግዚአብሔር እርሱ አምላክ ነው አሉ።ኤልያስም። ከበኣል ነቢያት አንድ ሰው እንዳያመልጥ ያዙ አላቸው። ያዙአቸውም፤ ኤልያስም ወደ ቂሶን ወንዝ ወስዶ በዚያ አሳረዳቸው።” 1 ነገ 18:17_40
“ በመካከልህም ነቢይ ወይም ሕልም አላሚ ቢነሣ፥ ምልክትም ተአምራትም ቢሰጥህ፥እንደ ነገረህም ምልክቱ ተአምራቱም ቢፈጸም፥ እርሱም። ሄደን የማታውቃቸውን ሌሎች አማልክት እንከተል እናምልካቸውም ቢልህ፥አምላካችሁን እግዚአብሔርን በፍጹም ልባችሁ በፍጹምም ነፍሳችሁ ትወድዱት እንደ ሆነ ያውቅ ዘንድ አምላካችሁ እግዚአብሔር ሊፈትናችሁ ነውና የዚያን ነቢይ ቃል ወይም ያን ሕልም አላሚ አትስማ።አምላካችሁን አግዚአብሔርን ተከተሉ፥ እርሱንም ፍሩ፥ ትእዛዙንም ጠብቁ፥ ቃሉንም ስሙ፥ እርሱንም አምልኩ፥ ከእርሱም ጋር ተጣበቁ።” ዘዳ 13: 1_4
“ በመጨረሻው ዘመን እንደ ራሳቸው ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበት እንዲመጡ ይህን በፊት እወቁ፤ እነርሱም። የመምጣቱ የተስፋ ቃል ወዴት ነው? አባቶች ከሞቱባት ጊዜ፥ ከፍጥረት መጀመሪያ ይዞ ሁሉ እንዳለ ይኖራልና ይላሉ። ሰማያት ከጥንት ጀምረው ምድርም በእግዚአብሔር ቃል ከውኃ ተጋጥማ በውኃ መካከል እንደ ነበሩ ወደው አያስተውሉምና፤ በዚህም ምክንያት ያን ጊዜ የነበረ ዓለም በውኃ ሰጥሞ ጠፋ፤ አሁን ያሉ ሰማያትና ምድር ግን እግዚአብሔርን የማያመልኩት ሰዎች እስከሚጠፉበት እስከ ፍርድ ቀን ድረስ ተጠብቀው በዚያ ቃል ለእሳት ቀርተዋል። እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፥ በጌታ ዘንድ አንድ ቀን እንደ ሺህ ዓመት፥ ሺህ ዓመትም እንደ አንድ ቀን እንደ ሆነ ይህን አንድ ነገር አትርሱ። ለአንዳንዶች የሚዘገይ እንደሚመስላቸው ጌታ ስለ ተስፋ ቃሉ አይዘገይም፥ ነገር ግን ሁሉ ወደ ንስሐ እንዲደርሱ እንጂ ማንም እንዳይጠፋ ወዶ ስለ እናንተ ይታገሣል። የጌታው ቀን ግን እንደ ሌባ ሆኖ ይመጣል፤ በዚያም ቀን ሰማያት በታላቅ ድምፅ ያልፋሉ፥ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይቀልጣል፥ ምድርም በእርስዋም ላይ የተደረገው ሁሉ ይቃጠላል። ይህ ሁሉ እንዲህ የሚቀልጥ ከሆነ፥ የእግዚአብሔርን ቀን መምጣት እየጠበቃችሁና እያስቸኰላችሁ፥ በቅዱስ ኑሮ እግዚአብሔርንም በመምሰል እንደ ምን ልትሆኑ ይገባችኋል? ስለዚያ ቀን ሰማያት ተቃጥለው ይቀልጣሉ የሰማይም ፍጥረት በትልቅ ትኵሳት ይፈታል፤ ነገር ግን ጽድቅ የሚኖርባትን አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር እንደ ተስፋ ቃሉ እንጠብቃለን። ስለዚህ፥ ወዳጆች ሆይ፥ ይህን እየጠበቃችሁ ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ ሆናችሁ በሰላም በእርሱ እንድትገኙ ትጉ፥ የጌታችንም ትዕግሥት መዳናችሁ እንደ ሆነ ቍጠሩ። እንዲህም የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ፥ በመልእክቱም ሁሉ ደግሞ እንደ ነገረ ስለዚህ ነገር ተናገረ። በእነዚያ ዘንድ ለማስተዋል የሚያስቸግር ነገር አለ፥ ያልተማሩትና የማይጸኑትም ሰዎች ሌሎችን መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ እነዚህን ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ። እንግዲህ እናንተ፥ ወዳጆች ሆይ፥ ይህን አስቀድማችሁ ስለምታውቁ፥ በዓመፀኞቹ ስሕተት ተስባችሁ ከራሳችሁ ጽናት እንዳትወድቁ ተጠንቀቁ፤ነገር ግን በጌታችንና በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና እውቀት እደጉ። ለእርሱ አሁንም እስከ ዘላለምም ቀን ድረስ ክብር ይሁን፤ አሜን።” 2 ጴጥ 3
“ ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።” ፊሊጱስዩስ 4:6_7
imagesNFOLOXX9
“ እነሆ ከአዳም ጎድን አንድ አጥንት ወጥታ እስከ አሁን ግን ትጠዘጥዘናለች”